የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ሥጋት አስተዳደርና የምርጫን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ማዕቀፍን የተመለከተ ዐውደ ጥናት አካሄደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትላንት ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ.ም. የሥጋት አስተዳደርና የምርጫን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ማዕቀፍን የተመለከተ ዐውደ ጥናት አካሄደ። በዐውደ ጥናቱ ላይ የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ሜላት ወርቅ ኃይሉን ጨምሮ አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት የተገኙ ሲሆን፤ የቦርዱ የየሥራ ክፍል ኃላፊዎችም ተገኝተዋል። ዐውደ ጥናቱን የቦርድ አመራር አባሏ ብዙወርቅ ከተተ በንግግር የከፈቱት ሲሆን፤ በንግግራቸውም ዐውደ ጥናቱ በዋናነት ዓላማው ያደረገው ቦርዱ ከሣምንታት በፊት ያስተዋወቀውንና ቦርዱ እንደአዲስ ከተቋቋመ ወዲህ መጀመሪያ የሆነውን የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድን በመተግበር ሂደት የተለያዩ ተግዳሮቶች ቢገጥሙት እንዴት ባለ’አግባብ ሣይንሳዊ መንገድን ተከትለን መፍታት እንችላለን፤ በዚህም ሂደት ማን ምን ሚና አለው የሚለውን መገምገምና መለየት በማስፈለጉ እንደሆነ አብራርተዋል።