Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አዲሱን አርማ ለሕዝብ ይፋ አደረገ

የካቲት 6 ቀን 2012 ዓ.ም.

የኢትዮጲያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ የሚያደርገው ውይይት ከመስከረም 27 እና 28 ቀን 2012 ዓ.ም. በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ከተደረገው የመጀመሪያው የባለድርሻ አካላት ኮንፈረንስ ቀጣይ ሲሆን የውይይቱም ዋና ዓላማ የመጪው አገራዊ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ማድረግ፣ ስለ ምርጫ ቦርዱ የሥራ እንቅስቃሴዎች እና ስለ 2012 አጠቃላይ ምርጫ ዝግጅት መረጃ ማካፈል፣ የምርጫ ዋና ዋና ተሳታፊዎች እና የትብብር ኃላፊነቶች እንዲሁም ስለቦርዱ ሥራዎችን በተመለከተ ውይይት ማድረግ ነው።

Share this post

​​የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከካናዳ መንግሥት ለተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም "የምርጫ ሥራ ድጋፍ ፕሮጄክት" የተሰጠውን ድጋፍ ዛሬ በጋራ ተፈራርሟል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከካናዳ መንግሥት ለተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም "የምርጫ ሥራ ድጋፍ ፕሮጄክት" የተሰጠውን ድጋፍ ዛሬ በጋራ ተፈራርሟል። በፊርማ ሥነ ስርዓቱ የቦርዱ አመራር አባላት ብዙወርቅ ከተተ እና አበራ ደገፋ (ዶ/ር) ተገኝተዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ) ህጋዊ ሰውነት ማጣትን በተመለከተ ውሳኔ ሰጠ

ኢህአዴግ በሊቀመንበሩ በኩል ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በላከው ደብዳቤ ግንባሩ መፍረሱን ለቦርዱ ያሳወቀ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ሕዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ (ሕወሃት) በሊቀመንበሩ በኩል በተጻፈ ደብዳቤ ግንባሩ በመፍረሱ የንብረት ክፍፍልን አስመልክቶ ቦርዱ ውሳኔ እንዲሰጥበት ጥያቄ አቅርበዋል። የግንባርን መፍረስ የመወሰን ሥልጣን የቦርዱ በመሆኑ ግንባሩም ሆነ ህወሃት ግንባሩ መፍረሱን መጥቀሳቸው የማይገባ ቢሆንም ቦርዱ ሁለቱ ሊቀመንበራት ያቀረቧቸውን የጽሁፍ ጥያቄዎ መሠረት በማድረግ ግንባሩ መፍረስ አለበት ወይ?

Share this post

  • ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ  e9
    ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ የቦርድ ሰብሳቢ
    ሜላትወርቅ ኃይሉ በተለያዩ የመንግሥትና የግል መሥሪያ ቤቶች ከ30 ዓመታት በላይ በማገልገል ልምድ ያላቸው ሲሆን፤ ከባለሞያነት ጀምሮ እስከ ከፍተኛ አመራርነት ሠርተዋል።
  • ነሲም አሊ e10
    ነሲም አሊ የቦርድ አባል
    ነሲም አሊ በመንግሥት ሥራ (በሕዝብ አገልግሎት) ለ10 ዓመት ገደማ በተለያዩ የፍርድ ቤት ዕርከኖች በዳኝነት በማገልገል ለሀገራቸው የፍትሕ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል፡፡
  • አቶ ተክሊት ይመስል e10
    ተኽሊት ይመሰል የቦርድ አባል
    አቶ ተኽሊት በመንግሥት ሥራ (በሕዝብ አገልግሎት) ከ25 ዓመታት በላይ የካበተ ልምድ አላቸው፡፡ አቶ ተክሊት በነዚኽ ዓመታት የዐቃቤ ሕግ መመሪያ ኃላፊ፣ የከፍተኛ እና የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ፣ የሠበር ሰሚ ችሎት ዋና ሰብሳቢ ዳኛ፣ የዳኞች አስተዳደር ጉባዔ አባል፣ እንዲሁም የከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ሆነው አገልግለዋል፡፡
  • አቶ ተስፋዬ ንዋይ e10
    ተስፋዬ ንዋይ የቦርድ ምክትል ሰብሳቢ
    አቶ ተስፋዬ ነዋይ በመንግሥት ሥራ (በሕዝብ አገልግሎት) ከ17 ዓመታት በላይ ማለትም በዐቃቤ ሕግነት፣ በሰብሳቢ ዳኝነት፣ በሕግ ጉዳዮች ተመራማሪነት እንዲሁም በዩንቨርስቲ መምህርነት አገልግለዋል፡፡ የኢትዮጵያ