ለፓርቲዎች የዕለት ተዕለት ሥራ ማገዣ በሚል መንግሥት የመደበውን 10 ሚሊየን ብር ሥራ ላይ እንዳላዋለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተናገረ
ግንቦት 8 ቀን 2011 ዓ.ም.
ለፓርቲዎች የዕለት ተዕለት ሥራ ማገዣ በሚል መንግሥት የመደበውን 10 ሚሊየን ብር ሥራ ላይ እንዳላዋለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተናገረ። ገንዘቡ ሥራ ላይ ቢውል ኖሮ ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ብቻ የሚጠቀምበት ይሆን ነበር። ፍትሃዊ ባልሆነ ምርጫ የምክር ቤቶችን ወንበር ሙሉ በሙሉ ለተቆጣጠረው ገዢው ፓርቲ ብቻ ገንዘቡን መስጠቱ አስፈላጊ ሆኖ አላገኘሁትም ብሏል ምርጫ ቦርድ። የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ እንዳሉት ከዚህ ቀደም በነበረው አሠራር መንግሥት ፓርቲዎችን ለማገዝ በሚል የሚመድበውን 10 ሚሊዮን ብር ፓርቲዎች በምክር ቤቶች ውስጥ ባላቸው መቀመጫ ልክ ገንዘቡ ይከፋፈላል የሚል አሠራር ነበር።