መልስ - የፓለቲካ ፓርቲዎች በሶስት አመት አንድ ጊዜ ከአባላት ጋር በመገናኘት ውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ አሰራራቸውን የሚያረጋግጡበት መንገድ ነው፡፡ ሶስት አመት ለጠቅላላ ጉባኤ አጠረ የሚባል አይደለም፡፡ አንድ ፓርቲ ከሶስት አመት በላይ ጠቅላላ ጉባኤ ሳያደርግ ከቆየ ውስጠ ፓርቲ አሰራሩ ላይ ያሉ ችግሮችንም በፍጥነት የመፍታት እድሉ ይጠባል፡፡ የአዋጁ አላማ ፓርቲዎችን አሰራር ማጠናከር፣ ውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲያቸውን ማበረታታት እና መቆጣጠር እንደመሆኑ መጠን ይህ አነስተኛ መስፈርት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

6