Skip to main content

የአዲሱ ምርጫ ሳጥን ስርጭት

ኅዳር 4 ቀን 2011 ዓ.ም.           

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዲሱ የምርጫና የፓለቲካ ፓርቲዎች ህግ 1162/2012 አንቀጽ 56 መሠረት የሚጠቀምባቸው የነበሩትን የድምፅ መስጫ ኮሮጆዎች በሚያሳይ ቁስ በተሠራ የምርጫ ሳጥን በመቀየር ለሲዳማ ሕዝበ ውሳኔ አፈጻጸም ለመጠቀም በስርጭት ዝግጅት ላይ ይገኛል።

 

Share this post

ጥብቅ ማሳሰቢያ ለሚዲያዎች በሙሉ

ጥቅምት 27 ቀን 2012 ዓ.ም.

የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔን ለመዘገብ የተዘጋጃችሁ እና የዘገባ ፍቃድ ለማግኘት የጠየቃችሁ የሚዲያ አካላት መታወቂያችሁን ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና መስሪያ ቤት እና ሀዋሳ የሚገኙ ሚዲያዎች ደግሞ ሀዋሳ ከሚገኘው የቦርዱ ጊዜያዊ ማስተባበሪያ መውሰድ እንደምትችሉ እንገልጻለን። ከቦርዱ ለሚዲያ የተዘጋጀውን መታወቂያ ሳይዙ የምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ መገኘት የምርጫ እና የፓለቲካ ፓርቲዎችን ህግ ጥሰት ሲሆን የምርጫ ጣቢያዎችን በማወክ በህግ የሚያስጠይቅ መሆኑን አጥብቀን እናሳስባለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post

የውይይት መድረክን ስለመሰረዝ

ጥቅምት 26 ቀን  2012 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔን ሲያከናውን ዋና ዋና ከሆኑት የምርጫ ተግባራት መካከል አንዱ የሆነውን መራጮች የሚገባውን መረጃ እንዲያገኙ የሚያስችላቸውን የምርጫ ቅስቀሳ ቀናት አሳውቆ እንደነበር ይታወቃል። ከዚህም በተጨማሪም ለሲቪል ማህበራት እና ለፓርቲዎች ጥሪ በማድረግ አስፈላጊውን የቅስቀሳ መድረክ እንደሚያዘጋጅ ገልጾ እንደነበርም ይታወሳል።

Share this post

የሲዳማ ህዝበ ውሳኔን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኃን በሙሉ የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ህዝበ ውሳኔን እያስፈጸመ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ በድርጊት መርሃ ግብሩ መሠረት የመራጮች ምዝገባ ጥቅምት 26 ቀን 2ዐ12 ዓ.ም ጀምሮ ኅዳር 6 ቀን 2ዐ12 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡ ሕዝበ ውሳኔውም ኅዳር 1ዐ ቀን 2ዐ12 ዓ.ም ይከናወናል፡፡ ይህንን ሂደት መከታተል የሚፈልጉ እና ህጋዊ ምዝገባ ያላቸው የመገናኛ ብዙኃን እስከ ማክሰኞ ጥቅምት 25 ቀን 2ዐ12 ዓ.ም እስከ ቀኑ 11 ሰዓት ከ30 ድረስ ለሥራው የሚመድቡትን ጋዜጠኛ (ቢበዛ ሁለት) ስም በጽሁፍ በማሳወቅ ፍቃድ ጥያቄ ማቅረብ ይችላሉ፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና መ/ቤት ቢሮ ቁጥር 5ዐ1 ድረስ በመምጣት ወይም የደብዳቤውን ስካን ቅጂ በቦርዱ ኢሜይል electionsethiopia [at] gmail.com በመላክ ጥያቄያችሁን እንድታቀርቡ እናሳስባለን፡፡  

የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ለማስፈጸም ህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚዎች ምልመላ

 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ለማስፈጸም ህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚዎች ምልመላ እያከናወነ እንደነበር ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ምዝገባ ሲያከናውን በቆየባቸው ቀናት የተገኘው የአመልካቾች ቁጥር መጨመር የተነሳ የህዝውሳኔ አስፈጻሚዎች ምዝገባን ዛሬ ያጠናቅቃል፡፡ በመሆኑም ለማመልከት የምትፈልጉ ዛሬ አርብ ጥቅምት 7 ቀን 2012 አ.ም እስከስራ ሰአት ማጠናቀቂያ (11 ሰአት) ድረስ ንፋስ ስልክ ቡና ቦርድ ጋር የሚገኘው የቦርዱ ማሰልጠኛ ማእከል ማመልከት የምትችሉ ሲሆን የማመልከቻው የመጨረሻ ቀን ዛሬ ነው፡፡

 

በድጋሚ የወጣ የህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚዎች ምልመላ ማስታወቂያ

 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ህዳር 2012 ዓ.ም ለሚያካሂደው የሲዳማ የክልልነት የመደራጀት ጥያቄ ህዝበ ውሳኔ 5500 (አምስት ሺህ አምስት መቶ) የሚሆኑ የህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚዎችን በበጎ ፍቃድ አበል ክፍያ ከአንድ ወር ላልበለጠ ጊዜ ለማሰራት ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል ነገር ግን በቂ የሆኑ አመልካቾች ስላልተገኙ ይህንን ማስታወቂያ በድጋሚ ለማውጣት ተገዷል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከመስከረም 27- 28 ያደረገው የሁለት ቀን ዓለም አቀፍ ጉባኤ ተጠናቀቀ

መስከረም 30 ቀን 2012 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከዩኤስኤድ እና ለዓለም አቀፍ የምርጫ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር “አገራዊ ምርጫ እና የምርጫ ባለድርሻ አካላት” በሚል ርእስ በምርጫ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያዘጋጀው የሁለት ቀን ኮንፍረንስ ተጠናቋል። በዚህ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ ከተለያዩ አገሮች የተጋበዙ እንግዶች ልምዳቸውን ያካፈሉ ሲሆን በቀጣዩ ምርጫ ሊታሰብባቸው የሚገባ ዋና ዋና አንኳር ጉዳዮችም ላይ ውይይት ተደርጓል። በክብርት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፕሬዘዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ጉባኤውን የከፈቱ ሲሆን መንግሥትን ጨምሮ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት አገርን በማስቀደም ለቀጣዮ ምርጫ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋእጾ እንዲያደርጉ ጥሪ አድርገዋል። ሚዲያ፣ ሲቪል ማህበራት እና ዜጎችም ሰላምን ባስጠበቀ ግጭትን በማያስነሳ መልኩ ተሳትፎ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

Share this post

የሲቪል ማህበራት ወኪሎች የተሳትፎ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ የክልልነት የመደራጀት ጥያቄ የህዝበ ውሳኔ አማራጮች አስተያየትና አመለካከቶች ከህዝብ የሚቀርብበት መድረክ ማመቻቸት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በዚህ ፕሮግራም ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ የሲቪክ ማህራትና በሲዳማ ዞን የምትንቀሳቀሱ የፓለቲካ ፓርቲዎች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጥቅምት 13 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ፍላሚንጎ ፊትለፊት የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ጽህፈት ቤት ወይም በሃዋሳ ከተማ በሚገኘው የቦርዱ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ድረስ በመቅረብ እንድትመዘገቡ ቦርዱ ያሳውቃል፡፡

የሲቪል ማህበራት ወኪሎች ለምዝገባ በምትቀርቡበት ወቅት የምትሰሩበትን ዘርፍ የሚያሳይ፣ ስልጣን ከተሰጠው አካል የተሰጣችሁን የማህበራት ምዝገባ ሰነድ ይዛችሁ መቅረብ እንደሚገባችሁ በዚህ አጋጣሚ በአክብሮት ይገልጻል፡፡

የህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚዎች ምልመላ ማስታወቂያ


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ህዳር 2012 ዓ.ም ለሚያካሂደው የሲዳማ የክልልነት የመደራጀት ጥያቄ ህዝበ ውሳኔ 6000 የሚሆኑ የህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚዎችን በበጎ ፍቃደኝነት ለአንድ ወር ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾች የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን ና ኮፒ በመያዝ ንፋስ ስልክ ቡና ቦርድ ፊትለፊት በሚገኘው የቦርዱ ማሰልጠኛ ማእከል በአካል በመገኘት ከመስከረም 24 ቀን 2012 ጀምሮ በስራ ሰአት እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡
አመልካቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች
• የማንኛውም የፓለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ያልሆነች
• በትምህርት ዝግጅታቸው በማንኛውም የትምህርት መስክ የመጀመሪያ ዲግሪ ያላት/ ያለው
• እድሜ ከ20- 45 አመት የሆነች/የሆነ
• በገጠር ቀበሌዎች ተንቀሳቅሰው መስራት የሚችሉ