የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ያለውን የመራጮች ምዝገባ ጣቢያዎች በተመለከተ የሰጠዉ ተጨማሪ መረጃ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ያለውን የመራጮች ምዝገባ ጣቢያዎች እጥረት ለማስተካከል እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል። በዚህም መሰረት ከቅዳሜ ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ተጨማሪ ጣቢያዎች በመክፈት የቀሩት የመራጮች ምዝገባ ቀናት የተሻለ ምዝገባ እንዲካሄድ ጥረት እያደረገ ይገኛል።
በመሆኑም በዚህ መሰረት ከስር በሚገኙት ዝርዝር አድረሻዎች መራጮች ምዝገባ ማከናውን እንደሚችሉ እየገለጽን ችግሮችን ሪፓርት ለማድረግ በነጻ የስልክ መስመራችን 778 በመደወል እንድታሳውቁን እንጠይቃለን።
በልዩ ሁኔታ በተለይ በጀሞ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ምርጫ ጣቢያዎችን ለመክፈት ለከተማ መስተዳድሩ በተደጋጋሚ ብናሳውቅም ከወረዳው ቢሮዎችን ማዘጋጀት ባለመቻሉ ከታቀዱት 15 አዳዲስ ጣቢያዎች 6ቱ መከፈት አልቻሉም። ይህንን ከወረዳው ያጋጠመንን ችግር ለመፍታት እየሰራን እንገኛለን።