Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ያለውን የመራጮች ምዝገባ ጣቢያዎች በተመለከተ የሰጠዉ ተጨማሪ መረጃ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ያለውን የመራጮች ምዝገባ ጣቢያዎች እጥረት ለማስተካከል እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል። በዚህም መሰረት ከቅዳሜ ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ተጨማሪ ጣቢያዎች በመክፈት የቀሩት የመራጮች ምዝገባ ቀናት የተሻለ ምዝገባ እንዲካሄድ ጥረት እያደረገ ይገኛል።

በመሆኑም በዚህ መሰረት ከስር በሚገኙት ዝርዝር አድረሻዎች መራጮች ምዝገባ ማከናውን እንደሚችሉ እየገለጽን ችግሮችን ሪፓርት ለማድረግ በነጻ የስልክ መስመራችን 778 በመደወል እንድታሳውቁን እንጠይቃለን።

በልዩ ሁኔታ በተለይ በጀሞ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ምርጫ ጣቢያዎችን ለመክፈት ለከተማ መስተዳድሩ በተደጋጋሚ ብናሳውቅም ከወረዳው ቢሮዎችን ማዘጋጀት ባለመቻሉ ከታቀዱት 15 አዳዲስ ጣቢያዎች 6ቱ መከፈት አልቻሉም። ይህንን ከወረዳው ያጋጠመንን ችግር ለመፍታት እየሰራን እንገኛለን።

Share this post

አጭር መረጃ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አገራዊ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን እያከናወነ እንደሆነ ይታወቃል። የመጀመሪያዎቹ ቀናት ላይ የነበረው ዝቅተኛ የመራጮች ምዝገባ ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መሻሻል ከማሳየቱም በላይ መራጮች በተለይ የምዝገባው ማጠናቀቂያ ቀናት ሲቃረቡ በከፍተኛ ሁኔታ እየተመዘገቡ እንደሆነ ይታወቃል።

ይህንን ተከትሎ በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ የጋራ መኖርያ ቤቶች አካባቢ ከፍተኛ ሰልፍ፣ የመራጮች ፍላጎት እና የምርጫ ጣቢያዎች አለመመጣጠን ተስተውሏል በመሆኑም ካለፈው ሳምንት አንስቶ ቦርዱ በልዩ ሁኔታ ችግሩን ለመፍታት እየሰራ ይህንን ተከትሎ የሚወስዳቸውን እርምጃዎቹን የሚያሳውቅ ይሆናል። በመሆኑም ለተፈጠረው የዜጎች መጉላላት ከፍተኛ ይቅርታ እየጠየቅን እርምጃዎቹን እስኪያሳውቅ ዜጎች እና አስፈጻሚዎች በትእግስት እንዲጠብቁን እናሳውቃለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእጩዎች ምዝገባን አስመልክቶ የተሰጠ መረጃ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእጩዎች ምዝገባ ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ የሚቀርቡ አቤቱታዎችን በመቀበል፣ ችግሮችን በመፍታት እንዲሁም የድምጽ መስጫ ወረቀት ቅደም ተከተል ሎተሪን በማከናወን የእጩዎችን ዝርዝር አጠናቆ ለድምጽ መስጫ ወረቀት ህትመት ሲያዘጋጅ ቆይቷል።

በምርጫ በፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና ስነምግባር አዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 39 (3) የፖለቲካ ፓርቲ እጩውን መለወጥ ወይም መተካት የሚቻልበት ቀን የእጩ ምዝገባ የጊዜ ሰሌዳ ካለቀ በኋላ ከሆነ ከድምጽ መስጫው ቀን ከአንድ ወር በፊት ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ እንደሆነ ይደነግጋል። በዚህም መሰረት ከዛሬ ከሚያዝያ 28 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ የእጩ መተካት፣ መቀየር፣ መለወጥ እና ማንኛውንም አይነት ማሻሻያ የማይቀበል መሆኑን ይገልጻል።

Share this post

የመራጮች ምዝገባ ሒደት ያልተጀመረባቸው የምርጫ ክልሎችን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መረጃ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን እያከናወነ እንደሆነ በምዝገባ ሂደቱም ወቅት የተለያዩ ሁኔታዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል። እንደሚታወቀው የመራጮች ምዝገባ በተወሰኑ ምርጫ ክልሎች መዘግየቱ የሚታወስ ነው። ቦርዱ ከክልል መስተዳድር አካላት ጋር ባደረገው ከፍተኛ የትብብር ስራ የምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው የመራጮች ምዝገባ ያልተጀመረባቸው ቦታዎች የመራጮች ምዝገባን ለማስጀመር ጥረት ሲያደርግ የቆየ

Share this post

የመራጮች ምዝገባ ሒደት ያልተጀመረባቸው የምርጫ ክልሎችን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መረጃ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን እያከናወነ እንደሆነ በምዝገባ ሂደቱም ወቅት የተለያዩ ሁኔታዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል። እንደሚታወቀው የመራጮች ምዝገባ በተወሰኑ ምርጫ ክልሎች መዘግየቱ የሚታወስ ነው። ቦርዱ ከክልል መስተዳድር አካላት ጋር ባደረገው ከፍተኛ የትብብር ስራ የምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው የመራጮች ምዝገባ ያልተጀመረባቸው ቦታዎች የመራጮች ምዝገባን ለማስጀመር ጥረት ሲያደርግ የቆየ ሲሆን በዚህም መሰረት የመራጮች ምዝገባ ከሚያዝያ 29 - ግንቦት 13 ቀን 2013 ድረስ በልዩ ሁኔታ እንዲከናወን ወስኗል።

ከነዚህም መሰረት

Share this post

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ አጭር መረጃ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ምርጫ አስፈጻሚዎችን በመቅጠር የምርጫ ስራን እያስፈጸመ እንደሆነ ይታወቃል። በዚህ ሂደት ውስጥ ካጋጠሙት ችግሮች መካከል አንዱ የሆነው የምርጫ አስፈጻሚዎች ክፍያ መዘግየት ነው። በተለያየ ወቅት የተለያዩ ክፍያዎች ሲደረጉ ቢቆዩም ከአስፈጻሚዎች ቅሬታ ሲያስነሳ የነበረ ጉዳይ መሆኑ አልቀረም።

Share this post

የመራጮች ምዝገባን የተመለከተ አጭር ማስታወቂያ

ለ6ተኛው አገራዊ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ እንደሆነ ይታወቃል፣ በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 በተደነገገው መሰረት የመራጮች ምዝገባ በብሔራዊ በአላት ቀናት አይከናወንም። በመሆኑም ነገ ሚያዝያ 22 ቀን 2013 ዓ.ም የስቅለት በአል በመሆኑ፣ ሚያዝያ 23 ቀን 2013 ዓ.ም የሰራተኞች ቀን በመሆኑ እና ሚያዝያ 24 ቀን 2013 ዓ.ም የፋሲካ በአል በመሆኑ ምርጫ ጣቢያዎች ዝግ ሆነው እነደሚውሉ ለማሳወቅ እንወዳለን። ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች ሰኞ ሚያዝያ 25

ለአካል ጉዳተኞች አጋዥ የምርጫ ቁሳቁሶች እና ትምህርት መሰጠት ተጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዐዋጅ እንደገና ከተቋቋመበት ጊዜ አንሥቶ በትኩረት እየሠራባቸው ካላቸው ተግባራት አንዱ የአካል ጉዳተኛና የሥርዓተ-ፆታ አካታችነት ተጠቃሽ ናቸው። ይህንንም ይረዳ ዘንድ የምርጫ ሕጉን ማዕቀፎች በዐይነ-ሥውራን ዘንድ ተዳራሽነቱን ለማስፋት ይረዳ ዘንድ ያሳተማቸውን ብሬሎች በአካል ጉዳተኞች የመራጮች ትምህርትና በመታዛቢነት ለተሠማሩ ለሲቪል ማኅበራት መስጠት ጀመረ።

ቦርዱ ብሬሎችን ከመስጠት በተጨማሪ በታዛቢነት ለተሠማሩ ሲቪል ማኅበራት ምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ ለሚኖራቸው ሕጋዊ እንቅስቃሴ ዕውቅና የሚያስገኝላቸውን ባጅ መስጠት ጀምሯል።

Share this post