Skip to main content

አንድ መራጭ ለክልል ምክር ቤት መቀመጫ ምን ያህል እጩዎችን መምረጥ ይችላል?

ለክልል ወይም ለከተማ ም/ቤት መቀመጫ አንድ መራጭ መምረጥ የሚችለው የእጩዎች ብዛት እንደየምርጫ ክልሉ ይለያያል ። አንዳንድ የምርጫ ክልሎች ላይ 1 እጩ፣ እንዳንድ የምርጫ ክልሎች ላይ 3 እጩዎች አንዳንድ የምርጫ ክልሎች ደግሞ ላይ 9 እጩዎች አንዳንድ የምርጫ ክልሎች ላይ 14 እጩዎች ወይም ሌላ ቁጥር ያለው የመቀመጫ ብዛት ሊኖራቸው ይችላል።

ብዛቱ የሚወሰነው የምርጫ ክልሉ በክልል ም/ቤቱ ባለው የመቀመጫ ቁጥር ብዛት ነው ። በመሆኑም አንድ መራጭ በክልል ም/ቤት ድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ መምረጥ የሚችለው የዕጩዎች ብዛት በክልል ምክር ቤት ድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ ከላይ ተፅፎ ይገኛል። በዚህም መሰረት አስፈጻሚዎች የድምፅ መስጫ ወረቀት ሲሰጡ ለመራጩ በምርጫ ጣቢያ ውስጥ እስከ ስንት እጩ መምረጥ እንደሚችል ያስረዳሉ።

ለምርጫ ክልል ምርጫ አስፈጻሚዎች በሙሉ

ሰኞ ሰኔ 14 ቀን ለሚከናውነው አጠቃላይ ምርጫ የፓርቲ ወኪሎችን እውቅና ባጅ የመስጠት ስራ እያከናወናችሁ እንደሆነ ይታወቃል። ካለው አጭር ጊዜ አንጻር የእጩ ወኪሎች ባጅ መስጠትን እስከ ነገ ማታ ሰኔ 13 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ እንድታከናውኑ እናሳስባለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኦፕሬሽንስ የስራ ክፍል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 11 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 11 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:30 በስካይ ላይት ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

  • በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣
  • የቦርዱን ልዩ የዘገባ ባጅ ፊት ለፊት ማንጠልጠል
  • ከአንድ ሚዲያ ሁለት ባለሞያዎች (የፎቶ/የቪዲዮ ባለሙያን ጨምሮ) ብቻ መሣተፍ ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 10 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 10 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:30 በስካይ ላይት ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

•በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣

•የቦርዱን ልዩ የዘገባ ባጅ ፊት ለፊት ማንጠልጠል

•ከአንድ ሚዲያ ሁለት ባለሞያዎች (የፎቶ/የቪዲዮ ባለሙያን ጨምሮ) ብቻ መሣተፍ ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

መረጃ ለግል እጩ ተወዳዳሪዎች

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከግል እጩ ተወዳዳሪዎች ጋር በተለያየ ግዜ ባደረገው ምክክር መሰረት ቦርዱ የግል እጩ ተወዳዳሪዎች የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው አምኖበት ለእያንዳንዳቸው የ50 ሺህ ብር ድጋፍ ለመስጠት ወስኗል፡፡

ስለሆነም በምርጫ ቦርድ በግል እጩ ተወዳዳሪነት እውቅና አግኝታችሁ ለ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ የምትወዳደሩ ሁሉ ሙሉ ስማችሁን አድራሻችሁን (ስልክ ቁጥራችሁን፣ ኢሜል) እንዲሁም የባንክ አካውንታችሁን ለፖለቲካ ፓርቲዎች ስራ ክፍል በአካል ወይም በ politicalparties@nebe.org.et ኢሜል አድራሻ ወይም በስልክ ቁጥሮች +251913551505/ +251929289444 የዋትስ አፕ እና ቴሌግራም አፕሊኬሽኖች ላይ እንድትልኩ እናሳውቃለን፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሰኔ 09 ቀን 2013 ዓ.ም

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 09 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 09 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:30 በስካይ ላይት ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

  • በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣
  • የቦርዱን ልዩ የዘገባ ባጅ ፊት ለፊት ማንጠልጠል
  • ከአንድ ሚዲያ ሁለት ባለሞያዎች (የፎቶ/የቪዲዮ ባለሙያን ጨምሮ) ብቻ መሣተፍ ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሰኔ 09 ቀን 2013 ዓ.ም

ስለ ጥሞና ወቅት መረጃዎች

የጥሞና ወቅት በቅድመ የምርጫ ዑደት ውስጥ የሚገኝ ጊዜ ሲሆን በኢትዮጵያ የምርጫ ዑደት መመሪያ መሠረት ምርጫ ከመደረጉ በፊት ያሉትን አራት ቀናት ያካትታል፡፡ በጥሞና ወቅት ታዲያ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት፤ ማለትም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመገናኛ ብዙሀን ተቋማት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ሀላፊነቶች አሉ፡፡

የፖለቲካ ፓርቲዎች

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 08 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 08 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:00 ሰዓት ባንቢስ ሱፐር ማርኬት ዐለፍ ብሎ በሚገኘው ዲ-ሊኦፖል ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። 

•በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣ 
•የቦርዱን ልዩ የዘገባ ባጅ ፊት ለፊት ማንጠልጠል
•ከአንድ ሚዲያ ሁለት ባለሞያዎች (የፎቶ/የቪዲዮ ባለሙያን ጨምሮ) ብቻ መሣተፍ ይችላሉ። 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሰኔ 08 ቀን 2013 ዓ.ም

Share this post

ለፓለቲካ ፓርቲዎች እና ለግል እጩዎች በሙሉ

የድምጽ መስጫ ቀን ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሆነ ይታወቃል። በመሆኑም የድምጽ መስጫ ቀን በምርጫ ጣቢያ በመገኘት የሚታዘቡ የፓርቲ ወኪሎቻችሁን እውቅና ለማሰጠት እና ባጅ ለማግኘት በምትወዳደሩበት ምርጫ ክልል ቢሮ በመሄድ ዝርዝራቸውን እንድታስገቡ እናሳውቃለን። ዝርዝር ማስገቢያው ቅጽ እና ቃለመሃላ ፎርም ከዚህ ማስታወቂያ ስር ተያይዟል።

የእጩ ወኪልነት መስፈርቶች

• በእጩ ወኪልነት የሚቀርብ/የምትቀርብ ማንኛውም ሰው የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት አለበት/አለባት።

1. ኢትዮጵያዊ ዜጋ የሆነ/ች፣

2. እድሜ 21 ዓመት እና ከዚያ በላይ የሆነ/ች፣

3. የመምረጥ እና መመረጥ መብቱ/ቷ በሕግ ያልተገደበ፣

4. የታወቀ ብልሹ ስነ-ምግባር የሌለበት/ባት፣

5. ማንበብ እና መፃፍ የሚችል/የምትችል እና

6. በእጩ ተወዳዳሪነት ያልተመዘገበ/ች መሆን አለበት/ባት፡፡

Share this post