የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ለሚካሄደው ድምፅ አሰጣጥ የመራጮች ምዝገባ በሚከናወንባቸው ቦታዎች የአስፈጻሚዎች ስልጠናዎችን አከናወነ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ለሚካሄደው ድምፅ አሰጣጥ የመራጮች ምዝገባን ለማከናወን ዝግጅቶቹን እያጠናቀቀ ነው። በዚህም መሰረት ለሁለት ተከታታይ ቀናት ማለትም ነሐሴ 22 እና 23 ቀን 2013 ዓ.ም ለሐረሪ ክልል፣ ነሐሴ 23 እና 24 ቀን 2013 ዓ.ም ደግሞ ለሶማሌ ክልል እና ለደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል ለመራጮች ምዝገባ ምርጫ አስፈጻሚዎች ሥልጠናዎችን ሰጥቷል።