የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች ምዝገባ ስልጠናዎችን አከናወነ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሁለት ተከታታይ ቀናት ማለትም የካቲት 26 እና 27 ቀን 2013 ዓ.ም ለመራጮች ምዝገባ የአሠልጣኞች ሥልጠና መስጠቱ ይታወሳል። የአሠልጣኞች ሥልጠናው ለምርጫ ክልል ኃላፊዎች፣ ለዞን አስተባባሪዎች፣ ለምርጫ ጣቢያ ሠራተኞችና ለልዮ ምርጫ ጣቢያ ሠራተኞች እንዲሁም ለመሥክ አሠልጣኞች ለመስጠት የታቀደው ሥልጠና አካል የነበረ ሲሆን፤ ለመሥክ አሠልጣኞቹ ደግሞ መጋቢት 4 እና 5 ቀን 2013 ዓ.ም ሥልጠናው ተሰጥቷል።