Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች ምዝገባ ስልጠናዎችን አከናወነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሁለት ተከታታይ ቀናት ማለትም የካቲት 26 እና 27 ቀን 2013 ዓ.ም ለመራጮች ምዝገባ የአሠልጣኞች ሥልጠና መስጠቱ ይታወሳል። የአሠልጣኞች ሥልጠናው ለምርጫ ክልል ኃላፊዎች፣ ለዞን አስተባባሪዎች፣ ለምርጫ ጣቢያ ሠራተኞችና ለልዮ ምርጫ ጣቢያ ሠራተኞች እንዲሁም ለመሥክ አሠልጣኞች ለመስጠት የታቀደው ሥልጠና አካል የነበረ ሲሆን፤ ለመሥክ አሠልጣኞቹ ደግሞ መጋቢት 4 እና 5 ቀን 2013 ዓ.ም ሥልጠናው ተሰጥቷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛዉን አጠቃላይ ምርጫ ለመታዘብ ለሲቪል ማህበራት እውቅና የመስጠት ስራውን አጠናቀቀ። 134,109 የአገር ውስጥ ታዛቢዎች ይሰማራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ስራውን አጠናቀቀ። 134,109 የአገር ውስጥ ታዛቢዎች ይሰማራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫን ለመታዘብ ፍላጎት ላላቸው የሀገር ዉስጥ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ፍቃድ ለማግኘት ማመልከቻዎቻቸውን እንዲያቀርቡ ባወጣዉ ማስታወቂያ መሰረት 111 ድርጅቶች እውቅናን ለማግኘት ያመለከቱ ሲሆን ድርጅቶቹ ያቀረቡትን ማመልከቻዎች እና ተያያዥ ሰነዶች በምርጫ ህጉ፣ በወጣዉ ጥሪ እና በመመሪያዉ የተደነገጉትን መስፈርቶች እና ግዴታዎች ያሟሉ ስለመሆኑ፣ እንዲሁም የድርጅቶቹ የማስፈፀም አቅም ተገምግሞ፣ እና በየደረጃዉ የተጓደሉ ሰነዶችን እንዲያሟሉ በማድረግ በመጀመሪያዉ ዙር ካመለከቱ ከ111 ድርጅቶች መካከል 43ቱ ድርጅቶች ወደ ሁለተኛዉ ዙር እንዲያልፉ ተደርጓል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዕጩዎች የምዝገባ ሂደትንና አጠቃላይ የኦፕሬሽን ሂደቶችን የተመለከተ የምክክር መድረክ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 8 ቀን 2013 ዓ.ም. የዕጩዎች የምዝገባና አጠቃላይ የኦፕሬሽን ሂደቶችን የተመለከተ የምክክር መድረክ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የብዙኃን መገናኛ አካላት በተገኙበት አካሄደ። ይህን የምርጫው የጊዜ ሠሌዳ ከወጣበት ጊዜ አንሥቶ በተከታታይና በልዩ ሁኔታ እየተደረጉ ያሉ የምክክር መድረኮች አካል የሆነውን መርኃ-ግብር በንግግር ያስጀመሩት የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ሲሆኑ፤ የዕጩዎች ምዝገባና ተያያዥ የኦፕሬሽን ሥራዎችን የተመለከቱ አጠቃላይ ገለጻ ሰጥተዋል። ግልጽነትና ፍትሐዊነትን ለመጨመር ያስችል ዘንድ በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የሚኖረውን የዕጩዎች ቅደም ተከተል በሎተሪ ዕጣ እንደሚወሠንም አክለው ገልጸዋል። የሰብሳቢዋን ማብራሪያ ተከትሎ የቦርዱ የኦፕሬሽን ክፍል ባልደረባ በዕጩዎች ምዝገባ ወቅት የቀረቡ አቤቱታዎችንና መልስ የተሰጠበትን አግባብ አብራርተው የተሣታፊዎች ሃሳብ አሰተያየት እንዲሰጡበት ተደርጓል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሴቶችን ያማከለ የምርጫ ቅስቀሳ ዘመቻ እና የባለድርሻ አካላት ሚናን አስመልክቶ የምክክር መድረክ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 6 ቀን 2013 ዓ.ም. ሴቶችን ያማከለ የምርጫ ቅስቀሳ ዘመቻ እና የባድርሻ አካላት ሚናን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ። መድረኩን የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ በንግግር የከፈቱት ሲሆን፤ ሰብሳቢው በንግግራቸው ያለፉት 30 ዓመታት የሴቶችን የፖለቲካ ተሣትፎ ምን እንደሚመስል ገልጸው ያለውን መሻሻል ጥናቶችን ጠቅሰው አብራርተዋል። መሻሻል ቢኖርም እንኳን ከሚፈለገውና ሊሆን ከሚገባው አንጻር እጅግ ብዙ እንደሚቀር አክለው ገልጸዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች ት/ት ፍቃድ ከተሰጣቸው ሲቪክ ማኅበራት ጋር ሁለተኛ ዙር ውይይት አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች ትምህርት ፍቃድ ከተሰጣቸው የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ጋር ሁለተኛ ዙር የውይይት መድረክ አካሄደ። በቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ የተከፈተው መድክ በተከታታይ ለሁለት ቀናት የተካሄደ ሲሆን መጋቢት 3 ቀን 2013 ዓ.ም.

Share this post

  • Fikre Gebrehiwot member
    ፍቅሬ ገ/ሕይወት የቦርድ አባል
    አቶ ፍቅሬ ገ/ሕይወት ከአምስቱ የቦርድ አመራር አንዱ ናቸው። አቶ ፍቅሬ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በሕግና በታሪክ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያገኙ ሲሆኑ፤ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በልማት ጥናቶችና በፕሮጀክት አስተዳደር አግኝተዋል።
  • የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ስጋት ከግምት ውስጥ ያስገባ ምርጫ ለማከናወን እየሰራ ነው

    ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ሊካሄድ የነበረው 6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስጋት ምክንያት ሊከናወን አለመቻሉ ይታወሳል። ቦርዱ በአሁኑ ወቅት በምርጫ ወቅት የኮቪድ-19 ስርጭትን በመከላከል ረገድ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶችን ለማከናወን ይረዳ ዘንድ የኮቪድ-19 አስተባባሪ ቀጥሮ የተለያዩ ተግባራትን እየፈጸመ ነው።

    ከእነዚህም ውስጥ በምርጫ ወቅት የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር አዘጋጅቶ ያጸደቀው መመሪያ አንዱ ሲሆን በዚህ መመሪያ ዙሪያ ከፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር ተደጋጋሚ የጋራ ምክክር መድረክ አከናወኗል። ከዚህም በተጨማሪ የሰራቸው ስራዎች የሚከተሉት ናቸው።

    Share this post

    ምርጫ ቦርድ ተጨማሪ የምርጫ አስፈጻሚዎችን ለመመልመል የወጣ ማስታወቂያ

    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛው አጠቃላይ ምርጫን ለማስፈጸም 140 ሺህ በላይ አስፈጻሚ ለመሆን የሚችሉ ሰዎቸን ምልመላ የሚያከናውንበት ሂደት በማጠናቀቅ የአስፈጻሚዎችን ፍቃደኝነትን፣ ገለልተኝነትን እና ብቃትን በማረጋገጥ ስራ ላይ አንደሆነ ይታወቃል።

    ምርጫ አስፈጻሚዎች የምርጫ ሂደቱ ዋና አካል መሆናቸውን በመረዳት እና ስራውም ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚጠይቅ በመሆኑ እንዲሁም የምርጫ ሂደቱ ከተጀመረ በኋላ የሰው ሃይል እጥረት እነዳይፈጠር በማሰብ ተጨማሪ የሰው ሃይል ምልመላ ማከናወን እንዳለበት አምኗል።

    በዚህም መሰረት

    - ለምርጫ አስፈጻሚነት በገለልተኝነት አገራችሁን ለማገልገል የምትፈልጉ

    - ምንም አይነት ፓርቲ አባልነት፣ የዝቅተኛ የአስተዳደር እርከኖች ላይ ሰርታችሁ የማታውቁ

    - ከሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ውጪ በሌሎች የቀድሞ ምርጫ የማስፈጻም ተግባራት ላይ ተሳትፋችሁ የማታውቁ

    - የመጀመሪያ ዲግሪ ወይም ተመጣጣኝ ረጅም አመት የስራ ልምድ ያላችሁ