Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 2ተኛ ሰበር ሰሚ ችሎት የወሰነውን ውሳኔ አስመልክቶ ዝርዝር የአፈጻጸም ማብራሪያ የጠየቀበት ጽሁፍ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 2ተኛ ሰበር ሰሚ ችሎት የወሰነውን ውሳኔ አስመልክቶ ዝርዝር የአፈጻጸም ማብራሪያ የጠየቀበት ጽሁፍ ከስር ከሚገኘው ሊንክ ላይ ማግኘት ይቻላል።

ደብዳቤዉን ለማግኘት  እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የክልል መስተዳድሮች ማድረግ ስለሚገባቸዉ ትብብር በሚመለከት የፃፈዉ ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ለሚከናወነው የድምጽ መስጫ ቀን ዝግጅቶቹን እያጠናቀቀ ይገኛል። በመራጮች ምዝገባ ወቅት ካጋጠሙት የትራንስፓርት እና የሎጄስቲክስ ችግሮች ትምህርት በመውሰድ ከክልል መንግስታት ጋር በመነጋገር ለድምጽ መስጫ ቀን የሚያስፈልጉትን እገዛዎች እያስተባበረ ነው።

በዚህም መሰረት ቦርዱ ለክልል መስተዳድሮች ድምጽ መስጫ ቀን ሊያቀርቡት የሚገባውን የትራንስፓርት ትብብር ግዴታ በዝርዝር በጽኁፍ ያሳወቀ ሲሆን ይህም የድምጽ መስጫው ቀን በታቀደለት ሁኔታ እንዲፈጸም ወሳኝ ተግባር ነው። በየክልሎቹ የሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር፣ አስፈላጊውን የመጓጓዥ ብዛት እና ቀኖች ትብብር ከስር በተያያዙት ደብዳቤዎች ላይ ይገኛል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለፖለቲካ ፓርቲዎች የደለደለዉ የገንዘብ ክፍፍል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከመንግስት የሚገኘውን የፓለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ ገንዘብ ለማከፋፈል መስፈርቶችን አውጥቶ እና ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር በማከናወን መወሰኑ ይታወሳል። በዚህም መሰረት

  • እኩል እውቅና ላላቸው የሚከፋፈል
  • ፓርቲው ባቀረበው እጩ ብዛት የሚከፋፈል
  • ፓርቲው ባቀረበው ሴት እጩ ብዛት የሚከፋፈል
  • ፓርቲው ባቀረበው አካልጉዳተኛ እጩ ብዛት የሚከፋፈል
  • ፓርቲው ባለው የሴት ስራ አስፈጻሚዎች ብዛት የሚከፋፈል መሆኑ በመመሪያው ላይ ተገልጿል።

የመጀመሪያው ዙር ክፍፍል የተጠናቀቀ ሲሆን ለፓርቲዎች የተደረገው አጠቃላይ የገንዘብ ክፍፍል ቀመር እና መስፈርት ዝርዝር በሚከተለው ሊንክ ላይ ይገኛል።

Share this post

መረጃ በሶማሌ ክልል እየተካሄደ ስላለው የመራጮች ምዝገባ ማጣራት ሂደት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም. የአውሮፓ ሕብረትና የጀርመን መንግሥት በጋራ ያበረከቱለትን 22 መኪኖች ተረከበ። የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ በተገኙበት የተፈጸመው ርክክብ 12 ሃርድ ቶፕ እና 10 ፒክ አፕ መኪኖችን ያካተተ ነው። ዋና ሰብሳቢዋ ቦርዱ የሎጀስቲክ እንቅስቃሴ ላይ ያለበትን ውስንነት ገልጸው ለተደረገው ድጋፍ ያላቸውን ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል። ቦርዱ በመንግሥትም ሆነ በአውሮፓ ሕብረት የሚደረጉለት ድጋፎች አስፈላጊነት ገልጸው፤ ለዛም ቦርዱ አመስጋኝ ነው ብለዋል።

Share this post

ስለምርጫ ቃላቶች በጥቂቱ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በብዛት የሚጠቀማቸው ከምርጫ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ቃላቶች የተወሰኑት እንደሚከተሉት ተዘርዝረዋል፡፡

#በምርጫብቻ

hfhh

 

Share this post

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእጩዎች ምዝገባን አስመልክቶ የቀረቡ አቤቱታዎች እና የተሰጡ ምላሾች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፓለቲካ ፓርቲዎች በተመዘገቡ እጩዎች ላይ ያላቸውን ቅሬታ እና አቤቱታ ሲቀበል መቆየቱ ይታወሳል። በዚህም መሰረት ዋና ዋናዎቹ ውሳኔ የተሰጠባቸው አቤቱታዎች የሚከተሉት ናቸው።

1. የዎላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ በወላይታ ዞን አቃቤ ህግ በእጩነት ተመዝግበዋል ብሎ አቤቱታ የቀረበው ጥያቄ ቦርዱ ተቀብሎ ለብልጽግና ፓርቲ የአቃቤህግነት ስራቸውን መልቀቃቸውን ወይም አቃቤ ህግ መሆን አለመሆናቸውን የሚያሳይ ማስረጃ እንዲያቀርብ ቦርዱ ጠይቋል።

2. የጋምቤላ ህዝብ ነጻነት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ብልፅግና ፓርቲ ካቀረባቸው እጩዎች መካከል የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ቢሮ ሀላፊ እንደሆኑና ይህም ከሕጉ ጋር እንደሚቃረን በመግለፅ አቤቱታ አቅርበዋል። በዚህም መሰረት ቦርዱ ለብልጽግና ፓርቲ እጩው ስራውን መልቀቅ እንዳለባቸው ወይም እጩነታቸውን መተው እንደሚገባቸው ወስኖ ለፓርቲው አሳውቋል።

Share this post

6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ የምትወዳደሩ ፓለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ

የመራጮች ምዝገባ ከተጠናቀቀ በኋላ ባሉት10 ቀናት የመራጮች መዝገብ ይፋ ተደርጎ ፓርቲዎች፣ ታዛቢዎች እና የሚመለከታቸው አካላት ሲመለከቱት የቆዩ ሲሆን የመራጮች መዝገብ ይፋ ማድረግ ሂደት በዛሬው እለት ተጠናቋል። ቦርዱ የመራጮች መዝገብ ይፋ ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ የመጡ አቤቱታዎችን ከፓርቲዎች በመተባበር ለመመርመር እና ለመፍታት ሙከራ ሲያደርግ ቆይቷል። አሁን ግን የመራጮች ምዝገብ ይፋ ማድረጊያ ጊዜ በመጠናቀቁ ፓርቲዎች በሂደቱ የታዘባችሁትን እና መፈታት አለበት የምትሉትን አቤቱታ የምርጫ ክልል እና ጣቢያን በማካተት እስከ ነገ ማታ 11፡30 ድረስ ለቦርዱ እንድታስገቡ እየጠየቅን ቦርዱ የቀረቡለት አቤቱታዎችን ለመመርመር እና ለመፍታት ከፍተኛ ጥረት የሚያደርግ መሆኑን እንገልጻለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

በስራ ላይ ለምትገኙ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ አስፈጻሚዎች በሙሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለድምጽ መስጫ ቀን አስፈጻሚነት ተጨማሪ አስፈጻሚዎችን እየመለመለ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ተጨማሪ የአስፈጻሚዎች ምልመላ በስራ ላይ ያላችሁ አስፈጻሚዎችን የማይጨምር ሲሆን አሁን ይፋ በሆነው ማመልከቻ ማመልከት አይጠበቅባችሁም።

በመሆኑም የአስፈጻሚዎች ማመልከቻ የወጣው አዲስ በአስፈጻሚነት ለመስራት ለሚፈልጉ እንጂ ከቦርዱ ጋር እየሰራችሁ ያላችሁትን የሚመለከት አለመሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

በሶማሌ ብሔራዊ ክልል ስለሚደረገው የመራጮች ምዝገባ አቤቱታ ማጣራት የተሰጠ ማስታወሻ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሚያዝያ 30 ቀን 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው በሶማሌ ብሔራዊ ክልል የሚገኙ የተለያዩ የፓለቲካ ፓርቲዎች የመራጮች ምዝገባ ሂደቱ ጉልህ የአሰራር እና የህግ ጥሰቶች አሉት በሚል አቤቱታ እና ማስረጃ ማቅረባቸውን፣ እንዲሁም የቀረቡት አቤቱታዎች እና ማስረጃዎች መሰረት አድርጎ ምርመራ ማድረግ እንደሚገባ ቦርዱ መገንዘቡን እና በዚህም መሰረት መጣራት እነደሚገባቸው በማመን በሰባት የምርጫ ክልሎች የመራጮች ምዝገባ በጊዜያዊነት እንዲቋረጥ በመወሰን የምዝገባ ሂደቱ ላይ የቀረቡ አቤቱታዎችን ማጣራት እንደሚያከናውን ማሳወቁ ይታወሳል።

Share this post