የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመከናወን ላይ የነበረውን የመራጮች ምዝገባ መጠናቀቅና ተያያዥ የሥራ ሂደቶችን አስመልክቶ ቦርዱ በነገው ዕለት ግንቦት 12 ቀን 2013 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ተኛው ሀገራዊ ምርጫ የጊዜ ሠሌዳ ከወጣበት ጊዜ አንሥቶ በልዩ ሁኔታ የተለያዩ መድረኮችን በማዘጋጀት የኦፕሬሽን ሥራዎችን ቅደም ተከተል በጠበቀ መልኩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በተለይም ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር እየመከረ ዛሬ ላይ መድርሱ ይታወቃል።