የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ ካፋ አረንጓዴ ፓርቲ (ካአፓ) መጋቢት 03 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ አስመልክቶ ተከታዩን ውሣኔ አሣልፏል
የተወነበት ቀን ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም.
መጋቢት 15 ቀን 2014 ዓ.ም. በቁጥር ካአፓ/1052/ በተጻፈ ደብዳቤ ፓርቲው መጋቢት 3 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ በሚመለከት ሪፖርት አቅርቧል።
ቦርዱ ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ ፓርቲው ከሪፖርቱ ጋር አያይዞ ያቀረባቸውን ሠነዶች ከሕጉ፣ ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ እና የቦርዱ ታዛቢዎች ካቀረቡት ሪፖርት አንጻር መርምሯል።
ጠቅላላ ጉባዔውን በተመለከተ
• በፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔ የተካሄደው የማዕከላዊ ኮሚቴ፤ የቁጥጥር ኮሚሽንና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ እጅ በማውጣት መደረጉ በዐዋጅ አንቀጽ 74(3) መሠረት ሚሥጥራዊ በሆነ መልኩ ያልተደረገ የሕጉን አስገዳጅ ድንጋጌ የተቃረነ በመሆኑ ፓርቲው ሕጉን መሠረት በማድረግ በድጋሚ ጠቅላላ ጉባዔ ሊካሄድ እንደሚገባ ቦርዱ ወሥኗል፡፡
የመተዳደሪያ ደንቡን በተመለከተ