Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ተኛው አጠቃላይ የምርጫ ሂደት ላይ የተደረገ የግምገማ ውጤት እንዲሁም የተገኙ ትምህርቶችን ማስተዋወቂያ እና ማጠናቀቂያ ዐውደ-ጥናት ዛሬ ሚያዝያ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ማካሄድ ጀምሯል፡፡

ቦርዱ የ6ተኛውን አጠቃላይ ምርጫ ተከትሎ በምርጫ ሂደቱ ላይ ከተገበራቸው የተለያዩ ተግባራት የተገኙ ትምህርቶችን የመሠነድ ተግባር ሲያከናውን የቆየ ሲሆን በሂደቱ የምርጫ ቦርድ አባላት፣ ሠራተኞች፣ የክልል ጽ/ቤት ሃላፊዎች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ታዛቢ ቡድኖች፣ የሲቪል ማኅበራት፣ የፊደራል እና የክልል የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የፍትሕ አካላት፣ የፀጥታ እና ሕግ አስከባሪ አካላት በተጨማሪም ከአጋዥ ድርጅቶች የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ኢንተርናሽናል ፋውንዴሽን ፎር ኤሌክቶራል ሲስተምስ (IFES) እና ዩሮፕያን ሴንተር ፎር ኤሌክቶራል ሰፓርት (ECES) በአጠቃላይ ከ400 በላይ ተሳታፊዎች ከተለያዩ የባላድርሻ አካላት በማካተት በየካቲት እና በመጋቢት ወራት ላይ ከ50 በላይ አነስተኛ የቡድን ውይይቶች፣ የምክክር መድረኮች፣ የቃል እና የጽሑፍ መጠይቆች ተከናውነዋል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ጠቅላላ ጉባኤ ማካሄዱን ተከትሎ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ ባደረገዉ ማሻሻያ ላይ ቦረዱ ያሳለፈዉ ዉሳኔ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ጠቅላላ ጉባኤ ማካሄዱን ተከትሎ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን ለቦርዱ ሪፓርት አቅርቧል፡፡ ቦርዱም ፓርቲው ያወጣውን ማሻሻያ ደንብ በመመርመር ያልተሟሉ ጉዳዮች ላይ ማስተካከያ እንዲያደርግ ውሳኔውን ያሳወቀበት ደብዳቤ ከስር ያገኙታል፡፡

  PDFእዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነፃነት ንቅናቄ ፓርቲ (ኦነን) ጠቅላላ ጉባኤውን አስመልክቶ የሰጠዉ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነፃነት ንቅናቄ ፓርቲ (ኦነን) ጠቅላላ ጉባኤውን አስመልክቶ የቀረቡ አጠራጣሪ ሰነዶችን አስመልክቶ ምርመራ እንዲደረግ ለፌደራል ፓሊስ ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን ምርመራው ተጣርቶ እስኪጠናቀቅ ፓርቲው በአዋጅ 1162/2011 አንቀፅ 98/3 መሰረት መታገዱን ይገልፃል።

 PDFደብዳቤዉን ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ባካሄደው ምክክር ወቅት ይፋ ያደረገው ለፓርቲዎች የሚሰጥ የገንዘብ ድጋፍ መጠን ከስር ይገኛል። የገንዘብ ድጋፉ ከዚህ ቀደም በፀደቀው መመሪያ ላይ በተቀመጡ መስፈርቶች መሰረት የተከናወነ ነው።

 PDFየገንዘብ ድጋፍ መጠን ለማግኘት አዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኦነግ አመራሮች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት አስመልክቶ ያሳለፈዉ ዉሳኔ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኦነግ አመራሮች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት አስመልክቶ የቀረቡለትን አቤቱታዎች በማየት ውሳኔ መስጠቱ ይታወሳል። በውሳኔው ቅር የተሰኙት የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር እነ አራርሶ ቢቂላ ጉዳዮን ወደፍርድ ቤት በመውሰዳቸው ክርክር ሲደረግበት ቆይቶ የሰበር ሰሚ ችሎት የሁለቱንም ወገኖች የመሰማት መብት በመጠበቅ አስተዳደራዊ ውሳኔ እንዲሰጥበት ወደቦርዱ መልሶታል። በዚህም መሰረት ቦርዱ የተለያዩ ምርመራዎችን በማድረግ የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ ተከትሎ ያሳለፈው ውሳኔ የሚከተለው ሲሆን ለሁለቱም ተከራካሪ ቡድኖች እንዲደርስ ተደርጓል።

Share this post

የስራ ቅጥር ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአዲስ አበባ ዋና መስሪያ ቤት እና ለክልል ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶች በተለያዩ የስራ መደቦች ተፈላጊውን የስራ ችሎታ እና ልምድ የሚያሟሉ ስራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡ ፍላጎት ያላችሁ እና መስፈርቱን የምታሟሉ ሁሉ ከታች የሚገኘውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም እንድታመለክቱ እናበረታታለን፡፡

አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣ በ10 ቀናት ውስጥ በኢሜል አድራሻችን hr.dept [at] nebe.org.et ብቻ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

Share this post

ማብራሪያ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 26 የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርጉ ባስታወቀው መሰረት የፓርቲዎች የጠቅላላ ጉባኤ ሲያካሂዱና ለማካሄድም ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል። በዚህም መሰረት የፓርቲዎች የጠቅላላ ጉባኤ ሁኔታ ማጠቃለያ የሚከተለውን ይመስላል።

ጠቅላላ ጉባኤ ያካሄዱ ፓርቲዎች

  1. ብልጽግና ፓርቲ
  2. ህዳሴ ፓርቲ
  3. ካፋ አረንጓዴ ፓርቲ
  4. የጋምቤላ ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ

ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ በጊዜ ገደቡ መሰረት ቀን ያሳወቁ ፓርቲዎች

Share this post