የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ተኛው አጠቃላይ የምርጫ ሂደት ላይ የተደረገ የግምገማ ውጤት እንዲሁም የተገኙ ትምህርቶችን ማስተዋወቂያ እና ማጠናቀቂያ ዐውደ-ጥናት ዛሬ ሚያዝያ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ማካሄድ ጀምሯል፡፡
ቦርዱ የ6ተኛውን አጠቃላይ ምርጫ ተከትሎ በምርጫ ሂደቱ ላይ ከተገበራቸው የተለያዩ ተግባራት የተገኙ ትምህርቶችን የመሠነድ ተግባር ሲያከናውን የቆየ ሲሆን በሂደቱ የምርጫ ቦርድ አባላት፣ ሠራተኞች፣ የክልል ጽ/ቤት ሃላፊዎች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ታዛቢ ቡድኖች፣ የሲቪል ማኅበራት፣ የፊደራል እና የክልል የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የፍትሕ አካላት፣ የፀጥታ እና ሕግ አስከባሪ አካላት በተጨማሪም ከአጋዥ ድርጅቶች የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ኢንተርናሽናል ፋውንዴሽን ፎር ኤሌክቶራል ሲስተምስ (IFES) እና ዩሮፕያን ሴንተር ፎር ኤሌክቶራል ሰፓርት (ECES) በአጠቃላይ ከ400 በላይ ተሳታፊዎች ከተለያዩ የባላድርሻ አካላት በማካተት በየካቲት እና በመጋቢት ወራት ላይ ከ50 በላይ አነስተኛ የቡድን ውይይቶች፣ የምክክር መድረኮች፣ የቃል እና የጽሑፍ መጠይቆች ተከናውነዋል፡፡