Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ “በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 1133/2011” እና “በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011” መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመመዝገብ ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡

በዚኹ መሠረት እነአቶ ጌታቸው ረዳ ካሕሳይ “ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ወይም Tigray Democratic Solidarity Party (Solidarity)“ በሚል ስያሜ ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ያቀረቡ በመሆኑ፤ በዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 68 ንዑስ አንቀጽ 2 እና 3 መሠረት በፓርቲው ስም፣ ዐርማ ወይም ሌሎች ጉዳዮች ተቃውሞ ያለው ሰው፤ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከዛሬ ከጥቅምት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በ14 ቀናት ውስጥ ተቃውሞውን ለቦርዱ ጽሕፈት ቤት እንዲያቀርብ ቦርዱ ያሳውቃል፡፡

ቦርዱ በምርጫ መታዘብ ለሚሳተፉ የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች የበይነ-መረብ ምዝገባ እና መረጃ አያያዝ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ-ግብር አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለሚታዘቡ የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች በበይነ-መረብ አማካኝነት ምዝገባ እንዲያደርጉ እና መረጃ እንዲያደራጁ የሚያስችላቸውን የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ-ግብር ከጥቅምት 25-26 ቀን 2018 ዓ.ም. አካሄደ።

በበይነ-መረብ አማካኝነት የሚደረገው ምዝገባ እና የመረጃ አያያዝ ቀድሞ በተለምዷዊ ስርዓት ይከናወን የነበረውን አሰራር በዘመናዊ ስርዓት የቀየረ ነው። የግንዛቤ ማስጨበጫው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በበለጸገው የበይነ-መረብ መመዝገቢያ እና መረጃ መያዣው ላይ የራሳቸውን ግብዓት እንዲጨምሩበትም ያለመ ነው።

በበይነ-መረብ የሚደረገው ምዝገባ እና መረጃ አያያዝ፤ የመረጃዎችን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ እንደሚረዳ፣ በተገቢው ለመሰነድ እና የመረጃ ትንተና ለማዘጋጀት በእጅጉ ጠቃሚ እንደሆነ በመርሀግብሩ ላይ ተጠቅሷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ ሀገራት አቻ የምርጫ አስፈጻሚ ተቋማትን እና የ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ መልካም ተሞክሮዎችን የተመለከተ ልዩ መርኃ-ግብር አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ ሀገራት አቻ የምርጫ አስፈጻሚ ተቋማትን እና የ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ መልካም ተሞክሮዎችን የተመለከተ ልዩ መርኃ-ግብር አካሄደ። አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት፣ የየሥራ ክፍልና የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እንዲሁም ከፍተኛ ባለሞያዎች በተሣተፉበት መድረክ ላይ፤ የተለያዩ ሀገራትን ምርጫዎች በመታዘብ ወቅት የተገኙ ልምዶችን እንዲሁም ከምርጫ አስፈጻሚ ተቋማት ጋር በተደረጉ የአቻ-ላቻ ልምድ ልውውጦች የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በተመለከተ በሁነቶቹ ላይ ተሣታፊ በነበሩ የቦርዱ ባለሞያዎች አማካኝነት ገለጻ ተሰጥቷል። በተወካዮቹ የቀረቡትን መልካም ተሞክሮዎች ተከትሎ በቡድን በቡድን በመሆን ከሀገራቱ ተሞክሮዎች ውስጥ ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ተስማሚና ተፈጻሚ መሆን የሚችሉት የትኞቹ ናቸው የሚሉት ላይ በመወያየት ሃሳብ የቀረበ ሲሆን፤ የ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ መልካም ተሞክሮዎችን በተመለከተም እንዲሁ አጭር ዘጋቢ ፊልም በማሳየት፤ ነባር የቦርዱ ባለሞያዎች ሊወሰዱ ይገባል ስላሏቸ

Share this post

ቦርዱ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ረቂቅ የምርጫ ጊዜ ሠሌዳውን በተመለከተ ከመገናኛ ብዙኃን እና ከሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች ጋር ምክክር አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ረቂቅ የምርጫ ጊዜ ሠሌዳን በተመለከተ ከመገናኛ ብዙኃን እና ከሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች ጋር በትላንትናው ዕለት ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም.

Share this post

በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ሲደረግ የነበረው የክርክር የተግባር ልምምድ መድረክ ተጠናቀቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያዘጋጀውና ከጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ሲካሄድ የነበረው በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የነበረው የክርክር የተግባር ልምምድ መድረክ ተጠናቀቀ። ቦርዱ የ7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ለውይይት ማቅረቡን ተከትሎ መካሄድ የጀመረውና፤ ፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ የክርክር ጊዜ ፖሊሲዎቻቸውንና ፕሮግራማቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ሥልት እንዲያዳብሩበት ታስቦ የተዘጋጀውን መድረክ የመሩት፤ የሚዲያና የኮሚኒኬሽን ባለሞያ የሆኑት ብሌን ፍጹምና ጌታቸው ድንቁ (ፒ.ኤች.ዲ) ሲሆኑ፤ በእያንዳንዱ ክርክር ማጠቃለያ ላይ ባለሞያዎቹ ተከራካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎቹ የተከተሉት የክርክር ሥነ-ዘዴን ጠንካራና ደካማ ጎን በመለየት ሞያዊ ምክረ ሃሳብ አቅርበዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የመራጮች ትምህርት ለሚሰጡ 143 የሲቪል ማኅበራት የዕውቅና የምሥክር ወረቀት ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የመራጮች ትምህርት ለሚሰጡ 143 የሲቪል ማኅበራት የዕውቅና የምሥክር ወረቀት ሰጠ። ዛሬ ቅዳሜ ጥቅምት 15 ቀን 2018 ዓ.ም.

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር የተግባር ልምምድ የሚያደርጉበትን መድረክ ማካሄድ ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ጊዜ ክርክር የተግባር ልምምድ የሚያደርጉበትን መድረክ ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም ማካሄድ ጀመረ። ቦርዱ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳውን አስመልክቶ፤ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በተወያየ ማግሥት የተጀመረውንና እስከ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆየውን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም የክርክር ልምምዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፖሊሲዎቻቸውንና ፕሮግራማቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ሥልት እንዲያዳብሩበት፤ ቦርዱ በቀጣይ በሚያወጣው ፕሮግራምም የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ያላቸውን ፕሮግራምና ፖሊሲ ለመራጩ ሕዝብ በመገናኛ ብዙኃን አማራጮች በይፋ ከማቅረባቸው በፊት ልምድ የሚያዳብሩበት ጠቃሚ መድረክ እንደሚሆን ያላቸውን ዕምነት ገልጸዋል።

Share this post

ቦርዱ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳ አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተያዘው ዓመት ለማካሄድ ልዩ ልዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። ቦርዱ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳ በማስመልከት ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ተወካዮች ጋር ምክክር አድርጓል። ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳው የምርጫ ጽ/ቤቶችን ከማደራጀት ጀምሮ እስከ ይፋዊ የምርጫ ውጤት ማሳወቂያ ድረስ ያሉትን ተግባራት ያካተተ ነው።

Share this post

ቦርዱ በምርጫ መታዘብ ላይ ለሚሣተፉ የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች የምርጫ መታዘብ ሥነ-ዘዴን የተመለከተ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችለውን በርካታ የቅድመ-ዝግጅቶች ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል። ከነዚኸም ውስጥ መራጮች እና ዕጩዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ እንዲመዘገቡ የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋት በዋናነት ተጠቃሽ ሲሆን፤ ይኽን እና መሰል ተግባራትን ሲያከናውንም የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን ጨምሮ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦ በመሥራት ነው።

ቦርዱ በምርጫ መታዘብ ላይ ለሚሠማሩ የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች የምርጫ መታዘብ ዕቅድ ዝግጅት እና የግኝት ሪፖርት አቀራረብ ሥነ-ዘዴ ላይ ያተኮረ ሥልጠና በትላንትናው ከትላንት በስትያ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. ሰጠ።

Share this post