የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በማሻሻል ላይ ያለው ዐዋጅ ረቂቅን በሲቭል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና በመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች አስተቸ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ "የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ ቁጥር ቁጥር 1162/2011" ላይ ያደረገውን የዐዋጅ ማሻሻያ በተመለከተ ባሳለፍነው ሣምንት ለሁለት ተከታታይ ቀናት ለፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ለመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች በማቅረብ ማስተቸቱ ይታወቃል። ቦርዱ ይኽን ከባለድርሻ አካላት ጋር በረቂቅ ዐዋጁ ላይ የሚያደርገውን ውይይት ቀጥሎ በተያዘው ሣምንትም ማለትም ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም. የረቂቅ ዐዋጅ ማሻሻያን ለሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶችና ለመገናኛ ብዙኃኑ አከላት ተወካዮች በማቅረብ ከተሣታፊዎቹ ሃሳብ አስተያየት ተቀብሏል።