Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

ዓሲምባ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲን በተመለከተ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ ውሳኔ

እነ ዶሪ አስገዶም ዓሲምባ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ/ዓዴፓ/ በሚል ስያሜ በ26/2/2012 ዓ.ም የክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ ህጋዊ የእውቅና ጥያቄ ለቦርዱ አቅርበው በምዝገባ ሂደት ላይ የነበሩ ሲሆን፤ የፓርቲው ህጋዊ የእውቅና ፈቃድ ሂደት በአገራችን በተከሰተው ጦርነት ምክንያት ተቋርጦ ቆይቶ በኋላም እነ ሐጎስ ወልዱ በቁጥር ዓዴ-0027/15 በቀን 25/07/2015 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ተቋርጦ የነበረው ሂደት እንዲቀጥል በማለት አመልክተዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በድጋሚ በቁጥር ዓዴ-0032/15 በቀን 16/09/2015 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ጊዜያዊ የእውቅና ፈቃድ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት ለመስጠት ፈቃደኛ ለሆኑ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስልጠና ሰጠ።

የቦርዱ የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት የስራ ክፍል የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርትን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ ከተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በጋራ እየሰራ ይገኛል።

ትምህርቱን በመላው ሀገሪቱ በስፋት ተደራሽ ለማድረግ የበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት የሚሰጡ ወጣቶችን ከየክልሉ በመመልመል በየአካባቢያቸው ለማሰማራት እቅድ የያዘ ሲሆን በቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኩል ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለተውጣጡ 25 የሁለተኛ እና ሦስተኛ ዓመት ተማሪዎች ከሚያዝያ 4 እስከ 5 /2017 ዓ.ም የቆየ የሁለት ቀናት የመጀመሪያ ዙር ስልጠና ሰጥቷል።

Share this post

የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በምርጫ ሂደት ትርጉም ባለው አግባብ እንዲሳተፉ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ተጠየቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአካታችነት ማዕቀፍ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በ7ኛው ሀገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ በመራጭነት እና በተመራጭነት የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል።

ይህን ዕቅድ ዕውን ለማድረግ ቦርዱ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን የምርጫ ፍላጎት ለመለየት እና ተሳትፎ ለማሳደግ ኢስት አፍሪካ የተባለ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ቀጥሮ ሀገራዊ ጥናት በማስጠናት ላይ ይገኛል።

አጥኚ ድርጅቱ አጥንቶ ባቀረበው ረቂቅ የጥናቱ ግኝቶች ላይ ለመወያየት በተዘጋጀ የአንድ ቀን አውደ ጥናት ላይ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን በምርጫ ሂደት የማሳተፍ ትርጉም ያለው ስራ የቦርዱ ጏላፊነት ብቻ ሳይሆን፤ መንግስትን ጨምሮ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሠራር እና ትብብርን ይጠይቃል ብለዋል።

Share this post

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርት የስራ ክፍል ከቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት በክልሉ ከሚገኙ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር የወጣቶች የበጎ ፈቃድ ስልጠናን አስመልክቶ ምክክር አደረገ።

የቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት የሥራ ክፍል ባለሙያ በጋራ በመሆን በስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት ዙሪያ ከቦርዱ ጋር እየሰሩ ለሚገኙ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንዲሁም ከሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለተውጣጡ የተማሪ ተወካዮች ትምህርቱን በክልሉ ለሚገኙ ልዩ ልዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች በስፋት ማዳረስ ስለሚቻልበት ዘዴ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶቹ በበኩላቸው በሚቀጥለው ዓመት የሚደረገውን 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ታሳቢ ያደረገ እቅድ ነድፈው የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርትን በተጠናከረ መልኩ ለመስጠት ዝግጅት እንደሚያደርጉ የገለጹ ሲሆን የተማሪዎች ተወካዮች በበኩላቸው ትምህርቱን በየትምህርት ቤታቸው በሚገኙ ሚኒ ሚድያዎችና በየወቅቱ በሚደረጉ ሁነቶች ለተማሪዎች ለማሰራጨት ማቀዳቸውን ገልጸው ቦርዱ ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል። የቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የስነ ዜጋና መራጮች ትምህርት የስራ ክፍል ባለሙያ ትምህርቱን በዘላቂ

Share this post

የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የህትመት ውጤቶችን ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ለሚገኙ የትምህርት ተቋማት አስረከበ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ስራ ክፍል ዜጎች በምርጫ ሒደት እና በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዙሪያ ግንዛቤን ያገኙ ዘንድ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ትምህርቶች እና መረጃዎችን ተደራሽ ማድረግ ላይ እየሰራ ይገኛል። በዚህም መሰረት የስራ ክፍሉ በቦርዱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኩል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፤ ሆሣዕና ከተማ አሰተዳደር፣ ሀላባ ዞን፣ ሀድያ ዞን፣ ጉራጌ ዞን፣ ስልጤ ዞን እና፣ ከምባታ ዞን ውስጥ ለሚገኙ 30 የሁለተኛ ደረጃ እና መሠናዶ ትምህርት ቤቶች በአማርኛ ቋንቋ “ምርጫ በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ የተዘጋጁ በቁጥር 900 ቡክሌቶችን አስረክቧል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህጻናት ፓርላማ ምስረታ ሥልጠና እና ሙያዊ ድጋፍ ሰጠ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 102 መሰረት ምርጫን የማስፈጸም ሥልጣን የተጣለበት ገለልተኛ ተቋም ነው፡፡ በመሆኑም ዜጎች በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እና በምርጫ ሂደት ዙሪያ ግንዛቤን ያገኙ ዘንድ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ በዚህም መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህጻናት ፓርላማ ባካሄደው የምስረታ እና የሥራ አስፈጻሚዎች ምርጫ ላይ በቦርዱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኩል የምርጫ ኦፕሬሽን እና የሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍሎች ባለሙያዎች በምርጫ ሂደት እና በዴሞክራያዊ መብት ልምምድ ዙሪያ ሥልጠና ሰጥተዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የህትመት ውጤቶችን በሐረር ከተማና በአጎራባች የገጠር ከተሞች በሚገኙ የትምህርት ተቋማት አሰራጨ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ ዜጋና መራጮች ትምህርት የሥራ ክፍል ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ እና በዜጎች ተሳትፎ ዙሪያ የዜጎችን ግንዛቤ የሚያጎለብቱ መልእክቶችን የያዙ የህትመት ውጤቶችን ማዘጋጀትና ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ተደራሽ ማድረግ ነው። በዚህም መሰረት የሥራ ክፍሉ ከቦርዱ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት በአማርኛና በኦሮምኛ ቋንቋ የተዘጋጁ በቁጥር 2950 ቡክሌቶችን እንዲሁም 46 የብሬል ቡክሌቶችን በሐረር ከተማ ለሚገኙ የመንግስትና የግል ሁለተኛ ደረጃ ት/ት ቤቶች፣ ለከፍተኛ ት/ት ተቋማት፣ በአጎራባች የገጠር ወረዳ ለሚገኙ ት/ት ቤቶች እንዲሁም ለአንድ መስማትና ማየት የተሳናቸው ት/ቤት አሰራጭቷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተለየያዩ የኦሮሚያ ከተሞች ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች የስነ ዜጋና መራጮች ትምህርት ይዘት ያላቸው የህትመት ውጤቶችን አሰራጨ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት የሥራ ክፍል መራጮች በዕውቀት ላይ የተመሠረተ ምርጫ እንዲያካሂዱ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ ሂደት ዙሪያ የሚያጠነጥኑ የተለያዩ መልዕክቶችን የያዙ የህትመት ውጤቶች በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ የትምህርት ተቋማት እና የሕዝብ ቤተ-መጻሕፍት እያሰራጨ ተደራሽነቱን እያሰፋ ይገኛል። በዚህም ሂደት የሥራ ክፍሉ ከቦርዱ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመሆን በአማርኛና በኦሮምኛ ቋንቋ የተዘጋጁ በቁጥር 2160 የሚሆኑ በስነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ዙሪያ ያተኮሩ ብሮሸሮች፣ ቡክሌቶች፣ አዋጆች እንዲሁም የቦርዱ መልዕክት የታተመባቸው ቲሸርቶችን በኦሮሚያ ክልል በባቱና ሻሸመኔ ከተሞች በሚገኙ 18 ትምህርት ቤቶች ማሰራጨት ችሏል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሐረሪ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ፓርቲ ላይ መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም የሰጠው የእግድ ውሳኔ የተነሳ መሆኑን የወሰነበት ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሐረሪ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ፓርቲ ላይ መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም የሰጠው የእግድ ውሳኔ የተነሳ መሆኑን የወሰነበት ደብዳቤ ለማግኘት ኢዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post