የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለጋምቤላ እና ለጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በጎ፟-ፍቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠና ሰጠ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም የሥነ ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት በመስጠት ላይ መሆኑ ይታወቃል። ከነዚኽም አማራጮች አንዱ በተለያዩ ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች በሚገኙ ብሔራዊ ዩኒቨርስቲዎች ለሚማሩ በጎ-ፍቃደኛ ተማሪዎች ትምህርቱን በመስጠት በተዋረድ ለአካባቢያቸው ማኅበረሰብ ግንዛቤ እንዲፈጥሩ ማስቻል ይጠቀሳል። ቦርዱ በያዝነው ወር ለጋምቤላ እና ለጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በጎ-ፍቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠናውን የሰጠ ሲሆን፤ ቀደም ሲልም በአምስት የተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ለሚገኙ በጎ-ፍቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠናውን ሰጥቷል።