የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን የተመለከተ የማኅበረሰብ ቲያትር በአዲስ አበባ ከተማ አቀረበ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን የተመለከተ የማኅበረሰብ ቲያትር በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙት በኮከበ ጽባሕ እና በከፍተኛ 12 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች፤ እንዲሁም “በጃንሜዳ የስፖርትና የሥልጠና ማዕክል” እና በመዲናዋ ከፍተኛ የሕዝብ እንቅስቃሴ ከሚበዛባቸው አካባቢዎች አንዱ በሆነው በመገናኛ አካባቢ አቀረበ።
በከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ ውስጥ በቀረበው ቲያትር ላይ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል የሚገኙ ተማሪዎች፣ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች የተገኙ ሲሆን፤ በቲያትሩም ላይ ስለምርጫ ሥነ-ባህሪያት፣ ስለመሠረታዊ የዴሞክራሲ ጽንሰ-ሐሳብና መርኆዎች፣ ስለማኅበራዊ አካታችነትና አካል ጉዳተኝነት ዲሞክራሲ ለዜጎች የሚያስገኘውን መብት ተግባራዊ ከማድረግ ሊገድበን እንደማይገባ እያዝናና የሚያስተምር መልዕክት ተላልፎበታል።