ዓሲምባ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲን በተመለከተ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ ውሳኔ
እነ ዶሪ አስገዶም ዓሲምባ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ/ዓዴፓ/ በሚል ስያሜ በ26/2/2012 ዓ.ም የክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ ህጋዊ የእውቅና ጥያቄ ለቦርዱ አቅርበው በምዝገባ ሂደት ላይ የነበሩ ሲሆን፤ የፓርቲው ህጋዊ የእውቅና ፈቃድ ሂደት በአገራችን በተከሰተው ጦርነት ምክንያት ተቋርጦ ቆይቶ በኋላም እነ ሐጎስ ወልዱ በቁጥር ዓዴ-0027/15 በቀን 25/07/2015 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ተቋርጦ የነበረው ሂደት እንዲቀጥል በማለት አመልክተዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በድጋሚ በቁጥር ዓዴ-0032/15 በቀን 16/09/2015 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ጊዜያዊ የእውቅና ፈቃድ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡