ቦርዱ በምርጫ መታዘብ ላይ ለሚሣተፉ የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች የምርጫ መታዘብ ሥነ-ዘዴን የተመለከተ ሥልጠና ሰጠ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችለውን በርካታ የቅድመ-ዝግጅቶች ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል። ከነዚኸም ውስጥ መራጮች እና ዕጩዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ እንዲመዘገቡ የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋት በዋናነት ተጠቃሽ ሲሆን፤ ይኽን እና መሰል ተግባራትን ሲያከናውንም የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን ጨምሮ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦ በመሥራት ነው።
ቦርዱ በምርጫ መታዘብ ላይ ለሚሠማሩ የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች የምርጫ መታዘብ ዕቅድ ዝግጅት እና የግኝት ሪፖርት አቀራረብ ሥነ-ዘዴ ላይ ያተኮረ ሥልጠና በትላንትናው ከትላንት በስትያ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. ሰጠ።