የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫና በድኅረ ምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን በተመለከተ አስጠንቶ ባጠናቀቀው ጥናት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ እና በድህረ ምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን በተመለከተ አስጠንቶ ባጠናቀቀው ጥናት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር መጋቢት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. ውይይት አካሄደ። ከጥናቱ መጠናቀቅ አስቀድሞ ፤ላለፉት ወራት ጥናቱን መሠረት ያደረጉ ውይይቶች ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ያካሄደ ሲሆን፤ በዚሁ በተጠናቀቀው ጥናት ላይ መጋቢት 12 በተደረገው ውይይት ደግሞ ከዚህ በፊት ያልተሳተፉ ግን የሚመለከታቸው ሲቪል ማኅበራትን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል።