የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ሥነ-ዘዴውን የተመለከተ ዐውደ-ጥናት አካሄደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አማካሪ ድርጅት ቀጥሮ ያሠራው የቦርዱን የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ሥነ-ዘዴ የገመገመ መነሻ ጥናት መጠናቀቁን ተከትሎ ግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም. ባካሄደው ዐዋደ-ጥናት፤ የጥናቱን ሂደትና ግኝት እንዲሁም ጥናቱን ተከትሎ የተሰጠውን ምክረ-ሃሳብ በአማካሪ ድርጅቱ ባለሞያዎች አማካኝነት ዐውደ ጥናቱ ላይ ተሣታፊ ለነበሩት የቦርዱ አመራሮች፣ ለሚመለከታቸው የቦርዱ ሥራ ክፍሎችና ባለድርሻ አካላት አቅርቧል።