Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ከፌዴራልና ከክልል የመገናኛ ብዙኃን ለተውጣጡ ጋዜጠኞች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ከፌዴራልና ከክልል የመገናኛ ብዙኃን ለተውጣጡ የዜና ክፍል ኃላፊዎች፣ አርታኢያን እና ጋዜጠኞች በገለልተኛ እና ሚዛናዊ የሚዲያ ዘገባ እና ኃቅን (እውነታን) በማረጋገጥ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጠ።

በሥልጠናው የመክፈቻ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ምርጫ ለሀገራችን ዲሞክራሲ ማበብ ዋና የማዕዘን ድንጋይ በመሆኑ የመገናኛ ብዙኃን የምርጫ ሂደት አዘጋገብ ከስሜት እና ከወገንተኝነት የፀዳ ሊሆን ይገባል ብለዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ2016 ዓ.ም. በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2017ዓ.ም. በጀት ዓመት ዕቅድን ከቦርዱ የአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ አንጻር የቃኘ መድረክ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 03 ቀን 2017 ዓ.ም የ2016 ዓ.ም. በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የቦርዱን የ2017 ዓ.ም.

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የብሬል ህትመት ዉጤቶችን ለኢትዮጵያ ዓይነ ሥዉራን ብሔራዊ ማህበር አስረከበ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትኩረት እየሠራባቸዉ ከሚገኙ ጉዳዮች መካከል ዜጎች ስለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እና የምርጫ ሂደት በቂ መረጃ እና ግንዛቤ የሚያገኙበትን አካታች ስልት መቀየስ እና የተለያዩ መገናገኛ ዘዴዎችን በመጠቀም የሥነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርት መስጠት ዋነኛዉ ተግባር ነዉ፡፡ በዚህም መሰረት የቦርዱ የሥነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ዓይነ-ሥዉራን ዜጎችን ተደራሽ ለማድረግ ይረዳ ዘንድ አምስት የተለያዩ ጉዳዮችን የያዙ ማለትም፤ የምርጫ ሒደት፣ ምርጫ በኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ ምን ዓይነት የምርጫ ሥርዓት ትከተላለች፣ ሰላማዊ ምርጫ በኢትዮጵያ፣ እና ዴሞክራሲ እና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በሚል አርዕስት በብሬል የተዘጋጁ 100 ብሮሸሮችን ለኢትዮጵያ ዓይነ ሥዉራን ብሔራዊ ማህበር አስረክቧል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች አካታችነትን በተመለከተ ሥልጠና አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መስከረም 14 ቀን 2017 ዓ.ም. የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች አካታችነትን በተመለከተ ሥልጠና አካሄደ። ይኽን ሁሉም የቦርዱ ሥራ ክፍል ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሞያዎች የተሣተፉበትን ሥልጠና በንግግር ያስጀመሩት የቦርድ አመራር አባሏ ብዙወርቅ ከተተ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች አካታችነት ሲባል ተፈናቃዮቹ እንደ መራጭ ያላቸውን መብት በማረጋገጥ ሳንወሠን እነሱን ዕጩ ተመራጭ ሆነው ጭምር እንዲመጡ የሚያስችል ሥራ መሠራት ጭምር እንደሆነ ተናግረዋል። ይኽም ሲባል የተፈናቃዮቹን ተሣታፊነት ለማረጋገጥ በወጡ ድንጋጌዎች መሠረት መሥራት ብቻ ሣይሆን የተለያዩ መለኪያዎችን በማስቀመጥ የሕጎቹን ተፈጻሚነት ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። አክለውም ቦርዱ በቅርቡ ባስተዋወቀው የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅዱ ላይ “ራዕይ” እና “ቁልፍ ዕሴቶች” ብሎ ከዘረዘራቸው ውስጥ አካታችነት አንዱ እንደሆነና ለቦርዱ አካታችነት ትልቁ ትኩረቱ መሆኑን ተናግረዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ጋር የምስጋና እና የልምድ ልውውጥ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ጋር የምስጋና እና የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሄደ። ቦርዱ በ6ኛው ሀገራዊ የቀሪና ድጋሚ ምርጫ በአፋር፣ በቤንሻንጉል-ጉሙዝ፣ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ዜጎች ስለዴሞክራሲያዊ ምርጫ እና ሂደቶች ግንዛቤ እንዲጨብጡ የስነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት እንዲያገኙ ብሎም በተለያዩ የስነ ዜጋ ትምህርት እሳቤዋች ዙሪያ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር የክርክር መድረኮች በማዘጋጀት በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት የክርክር ባህል እንዲጎለብት የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የሲቪል ማኅበራቱ የምስጋና እና የልምድ ልውውጥ አካሂዷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአካል ጉዳተኞች አካታችነት ላይ ሥልጠና አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቦርዱ ሥራ ክፍል ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሞያዎች የተሣተፉበትን ሥልጠና መርኅ-ግብር መስከረም 8 እና መስከረም 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ለሁለት ቀናት የአካል ጉዳተኞች አካታችነት ላይ ሥልጠና አካሄደ። ስልጠናዉን በንግግር ያስጀመሩት የቦርድ አመራር አባል የሆኑት ፍቅሬ ገ/ሕይወት ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ቦርዱ በተለይም በምርጫ ወቅት ትኩረት ሠጥቶ ከሚሠራባቸው ጉዳዮች ውስጥ የአካል ጉዳተኞች አካታችነት ከዋነኞቹ እንደ አንዱ የሚጠቀስ መሆኑን፤ ይኽም ሥልጠና ቦርዱ ለጉዳዩ የሚሰጠው ትኩረት በምርጫ ወቅት ብቻ የተገደበ ላለመሆኑ ማሳያ ነው ሲሉ ተናግረዋል። አመራሩ፤ በተጨማሪም አካል ጉዳተኛ የማኅበረሰብ ክፍሎች በምርጫ ወቅት በበቂ ላለመሣተፋቸው ምን ዓይነት ተግዳሮቶች አሉባቸው የሚለውን በመለየት የመፍትሔውም አካል መሆን እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በብሬይል የተዘጋጁ የተለያዩ የኅትመት ውጤቶችን ለኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሓፍት አገልግሎት አስረከበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከምርጫ ጋር ተያያዥነት ባላቸው በአምስት የተለያዩ አርእስቶች የተከፋፈሉ የብሬይል ብሮሸሮችንና ዐዋጆችን ለኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ነሐሴ 24 ቀን 2016 ዓ.ም. አስረከበ። በብሬይል ከተዘጋጁት ኅትመቶች ውስጥ ዴሞክራሲ እና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት፣ አካታች የሆነ የምርጫ ሂደት፣ ምርጫ በኢትዮጵያ፣ የኢትዮጵያ የምርጫ ሥርዓት እና ሰላማዊ ምርጫ በኢትዮጵያ የሚሉ አርእስቶች ይገኙበታል። ቦርዱ በተጨማሪም በብሬይል የተዘጋጀ ‘የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011’ን ለአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ አበርክቷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቀጠናዊ የምርጫ ሥጋት አስተዳደር ልምድ ልውውጥ አውደ ጥናት ላይ ተሣተፈ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዲስ አበባ በተካሄደው በቀጠናዊ የምርጫ ሥጋት አስተዳደር ልምድ ልውውጥ ላይ ተሣተፈ። ነሐሴ 20 እና 21 ቀን 2016 ዓ.ም. በተካሄደው ቀጠናዊ ልምድ ልውውጥ አውደ ጥናት ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአራት ሀገራት ማለትም ከኬንያ፣ ቦትስዋና፣ ማላዊና ሴራሊዮን የመጡ የምርጫ ቦርድ አመራሮችና ባለሞያዎች የተሣተፉ ሲሆን፤ የልምድ ልውውጥ መድረኩም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ተጀምሯል። ሰብሳቢዋ በመክፈቻ ንግግራቸው ይኽ ቀጠናዊ የሥጋት አስተዳደር የልምድ ልውውጥና ሥልጠና ሀገራቱ በምርጫ ጉዳይ ላይ ያላቸውን ዕውቀት፤ልምድ እንዲለዋወጡና አንዳቸው ከሌላቸው የተሻለ ተሞክሯቸውን እንዲወስዱ የሚያስችል መሆኑን፤ ይኽም እርስ በርስ በመደጋገፍ በጋራ ለማደግ እንደሚያስችል ገልጸዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ‘ለትንሳኤ ስርዓት ቓንጪ ሓቂ’ የክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ  ‘ለትንሳኤ ስርዓት ቓንጪ ሓቂ’   የክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ  የምስክር ወረቀት ሰጠ

Share this post