Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በማሻሻል ላይ ያለው ዐዋጅ ረቂቅን በሲቭል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና በመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች አስተቸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ "የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ ቁጥር ቁጥር 1162/2011" ላይ ያደረገውን የዐዋጅ ማሻሻያ በተመለከተ ባሳለፍነው ሣምንት ለሁለት ተከታታይ ቀናት ለፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ለመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች በማቅረብ ማስተቸቱ ይታወቃል። ቦርዱ ይኽን ከባለድርሻ አካላት ጋር በረቂቅ ዐዋጁ ላይ የሚያደርገውን ውይይት ቀጥሎ በተያዘው ሣምንትም ማለትም ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም. የረቂቅ ዐዋጅ ማሻሻያን ለሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶችና ለመገናኛ ብዙኃኑ አከላት ተወካዮች በማቅረብ ከተሣታፊዎቹ ሃሳብ አስተያየት ተቀብሏል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ - የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 - የረቂቅ አዋጅ ማሻሻያ ላይ ምክረ ሃሳብ ለመሰብሰብ ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና ከመገናኛ ብዙሃን ተወካዮች ጋር መከረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ላለፉት ስድሰት ዓመታት ስራ ላይ ያዋለውን የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ለማሻሻል በሁለት ዙሮች ለሁለት ቀናት በቆየ መርሃ-ግብር ከፓለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች እና ከመገናኛ ብዙሃን አመራሮች ጋር በመወያየት ጠቃሚ ግብዓቶችን መሰብሰብ ቻለ።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ታግዶ የማይሰረዝበትን መከላከያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ የወሰነበት ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ታግዶ የማይሰረዝበትን መከላከያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ የወሰነበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ ያደረገውን ጠቅላላ ጉባኤ ተቀብሎ ያፀደቀው መሆኑን የገለፀበት ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ ያደረገውን ጠቅላላ ጉባኤ ተቀብሎ ያፀደቀው መሆኑን የገለፀበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የቦርዱን የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ማስተባበሪያ ቢሮ የማቋቋም ፋይዳ

የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1133/2011 በአንቀጽ 23 እና 24 መሠረት ቦርዱ በሁሉም የሀገራችን ክልሎች ምርጫ የሚያስተባብሩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች እንደሚያቋቁም ይደነግጋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባልተማከለ የምርጫ አስተዳዳር ሥርዓቱ (Decentralized electoral administration) በምርጫ ዑደት ውስጥ ከቅድመ ምርጫ አንሥቶ እስከ ድኅረ ምርጫ ሒደቶች ድረስ ያሉትን ክንዋኔዎች ለህዝብ ተደራሽ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት ይረዳው ዘንድ በቦርዱ ዋና መ/ቤት የሚገኝ ራሱን ችሎ የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን የሚያስተባብር የሥራ ክፍል አቋቁሟል፡፡

Share this post

ቦርዱ ያዘጋጀውን የሥነ ዜጋና መራጮች ትምህርት ማስተማሪያ ማንዋልን ለማዳበር የሚረዳ አውደ ጥናት ተካሄደ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ድጋፍ በአማካሪ ተቋም ያስጠናውን በ 2013 ዓ.ም. ሀገራዊ ምርጫ ወቅት ሢሠራበት የነበረውን የሥነ ዜጋና መራጮች ትምህርት ማስተማሪያ ማንዋል የሲቪል ማኅበራት ድርጅት አመራሮች፣ ተወካዮች፣ የቦርዱ የፌደራል እና የክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊዎች እና የስነ-ዜጋና አካታችነት ባለሙያዎች በተገኙበት በመገምገም ሰነዱን የሚያዳብሩ ጠቃሚ ግብዓቶችን ሰበሰበ።

Share this post