Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ ሊደርስ የሚችል ጥቃትን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል የአሠራር ሥርዓት ሠነድ አፀደቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመከላከል የሚያስችል የአሠራር ሥርዓት (Standard Operating Procedure (SOP)) አፀደቀ። በአሠራር ሥርዓቱ ጥቃቱን በተመለከተ የትኞቹ ተቋማት ይመለከታቸዋል የሚለውን የባለድርሻ አካላት ልየታን ጭምር ያካተተ ሲሆን፤ ከነዚኽም ውስጥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙ`ኃን ባለሥልጣን፣ ለምርጫ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኅብረት፣ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እና የኢትዮጵያ ሴት የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ጥምረት ይጠቀሳሉ።

Share this post

ቦርዱ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫን በመታዘብ ላይ ለተሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከቦርዱ ዕውቅና አግኝተው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫን በመታዘብ ሥራ ላይ ለተሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባሳለፍነው ሣምንት መጠናቀቂያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ። የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር የቦርዱ ሰብሳቢ የሆኑት ሜላትወርቅ `ኃይሉ ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸውም ቦርዱ በቅድመ ምርጫ ተግባራቱ በርካታ ሥራዎችን ሲሠራ እንደነበር፤ ከዚኽም ውስጥ በምርጫ መታዘብ ሥራ ላይ ለሚሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ዕውቅና መስጠት አንዱ እንደሆነ አስታውሰው፤ ይኽም ከቅድመ ምርጫ እስከ ድኅረ-ምርጫ ያለውን ሦስቱንም የምርጫ ዑደቶች እንደሚያካትት ተናግረዋል።

Share this post

ቦርዱ ሥምሪት የሰጣቸው የክትትል ቡድኖች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸውን አካባቢዎች የፀጥታ ሁኔታን በተመለከተ ዝርዝር ሪፖርት አቀረቡ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም. 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት፣ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮችና የከተማ መስተዳድር ከንቲባዎች፣ የፌደራልና የክልል የፀጥታ ተቋማት አመራሮች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች በተገኙበት ውይይት ማካሄዱን ተከትሎ የአካባቢዎቹን የፀጥታ ሁኔታ አስመልክቶ የተለያዩ ውይይቶችን በተለያየ ጊዜ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሲያደርግ ቆይቷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሴት ፓለቲካ ፓርቲ እና የግል ተወዳዳሪ ዕጩዎችን ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ገለልተኛ፣ ተዓማኒና ሁሉን አካታች ለማድረግ የሚያስችለውን በርካታ የቅድመ ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። በዚኽም አግባብ ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ለሚወዳደሩ ሴት ፓለቲካ ፓርቲ እና የግል ዕጩዎች ሥልጠና ሰጥቷል።

ከሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ምርጫ በሚደረግባቸው በ13 ክልሎችና በሁለቱ ከተማ መስተዳድሮች በሚገኙ በ17 ከተሞች በተሰጠው ሥልጠና ላይ ከ1,731 በላይ ሴት ዕጩዎች የተሣተፉ ሲሆን፤ ዐላማውም ሴት ዕጩዎች በምርጫ ወቅት ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ፆታዊ ጥቃቶች መገለጫቸውና ምላሽ ስለሚሰጡበት ሕጋዊ አግባብ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ላይ በሚኖራቸው ተሣትፎና የዐደባባይ ላይ ንግግሮችን ሲያደርጉ ሊከተሏቸው ስለሚገቡ ሥነ-ዘዴዎች ግንዛቤ እንዲያገኙ ማስቻል ነው።

Share this post

ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አሁናዊ ሂደት ላይ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችንና መፍትሔዎቻቸውን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያየ

ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አሁናዊ ሂደት ላይ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችንና መፍትሔዎቻቸውን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ጋር ተወያየ። የውይይቱን መክፈቻ ንግግር የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸውም የስብሰባው ዋና ዐላማ ፖለቲካ ፓርቲዎቹ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እያደረጉ ባሉት ዝግጅት ላይ ያጋጠሟቸው ተግዳሮቶች ላይ ለመወያየትና የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ እንዲሁም ለድምፅ መስጫው ቀን በቀሩት ጥቂት ቀናት ከማን ምን ይጠበቃል በሚለው ላይ ለመወያየት መሆኑን ተናግረዋል።

Share this post

ቦርዱ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ትምህርት እንዲሰጡ ፍቃድ የሰጣቸው የሲቪል ማኅበረስብ ድርጅቶች ለተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የመራጮች ትምህርት ሰጡ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ትምህርት እንዲሰጡ የማሰተማሪያ ፍቃድ የሰጣቸው የሲቪል ማኅበረስብ ድርጅትች በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ፣ በሐረሪ፣ በአፋር፣ በሶማሌ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና በሲዳማ ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ ከተማ መስተዳድሮች ለሚገኙ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የመራጮች ትምህርት ሰጡ::

Share this post

ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመወዳደር ለተመዘገቡ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎችን ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድል ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በግል ዕጩነት ለመወዳደር የተመዘገቡ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎችን አወያይ። አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት የተገኙበትን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉን ሲሆን፤ በንግግራቸውም፤ ቦርዱ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በጊዜ ሠሌዳው መሠረት ለማካሄድ ልዩ ልዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን እያከናወነ መሆንኑ አስታውሰው፤ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድልም የዚኹ አካል መሆኑን ተናግረዋል። የውይይቱ አንዱ አጀንዳ የሆነው የነፃ የዓየር ሰዓት ድልድልን አስመልክቶ ሲናገሩም የግል ዕጩዎቹ በሚያደርጉት የምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ሕጉን ተከትለው በኃላፊነት ስሜት መሆን እንዳለበትና ይኽም የምርጫውን ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒነት በማረጋገጥ ረገድ ትልቅ ድርሻ እንዳለው ተናግረዋል።

Share this post

ቦርዱ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎች የፀጥታ ሁኔታን የሚከታተል ቡድንን ሥምሪትና ተግባራትን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎች የፀጥታ ሁኔታን የሚከታተል ቡድንን ሥምሪትና ተግባራትን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ። የውይይቱን የመክፈቻ ንግግር የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸውም ቦርዱ ቀደም ሲል ከመንግሥት የፀጥታ ተቋማ በመቀጠልም ከፖለቲካ ፓርቲዎች የተሰበሰበውን የፀጥታ ሁኔታ መረጃ መሠረት አድርጎ የተለያዩ ውይይቶችን ማካሄዱን አስታውሰው፤ የዚኽም ውይይት ዋና ዐላማ ቀደም ሲል የቀረቡ መረጃዎች መሬት ላይ ወርዶ በትክክል ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በመመልከት ሁኔታውን የሚመለከት የክትትል ቡድንን ሥምሪትና ተግባራት ላይ መወያየት በማስፈለጉ እንደሆነ ተናግረዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድል የዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድል የዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት አካሄደ። የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ በንግግራቸው ነፃ ዓየር ሰዓት ድልድሉን በዐዋጁ መሠረት ቦርዱ ከመገናኛ ብዙ`ኃን ባለሥልጣን ጋር በመሆን ለሣምንታት ሲያስተባብር እንደነበር ገልጸው፤ የሰዓት ድልድሉ ፖለቲካ ፓርቲዎች ፕሮግራማቸውንና ፖሊሲዎቻቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ የግል ዕጩዎችም አማራጭ ሀሳባቻቸውን እንዲያጋሩና የምርጫ ቅስቀሳ እንዲያደርጉ፣ ከመራጩ ጋር እንዲተዋወቁ ዕድል የሚሰጣቸው መሆኑን ተናግዋል። ይፋ የተደረገው ነፃ የዓየር ሰዓትን የተመዘገቡ 46 ፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች በኃላፊነት ስሜት እንዲጠቀሙበት በአፅንዖት አሳስበዋል።

Share this post