የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድል የዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት አካሄደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድል የዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት አካሄደ። የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ በንግግራቸው ነፃ ዓየር ሰዓት ድልድሉን በዐዋጁ መሠረት ቦርዱ ከመገናኛ ብዙ`ኃን ባለሥልጣን ጋር በመሆን ለሣምንታት ሲያስተባብር እንደነበር ገልጸው፤ የሰዓት ድልድሉ ፖለቲካ ፓርቲዎች ፕሮግራማቸውንና ፖሊሲዎቻቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ የግል ዕጩዎችም አማራጭ ሀሳባቻቸውን እንዲያጋሩና የምርጫ ቅስቀሳ እንዲያደርጉ፣ ከመራጩ ጋር እንዲተዋወቁ ዕድል የሚሰጣቸው መሆኑን ተናግዋል። ይፋ የተደረገው ነፃ የዓየር ሰዓትን የተመዘገቡ 46 ፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች በኃላፊነት ስሜት እንዲጠቀሙበት በአፅንዖት አሳስበዋል።