Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድል የዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድል የዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት አካሄደ። የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ በንግግራቸው ነፃ ዓየር ሰዓት ድልድሉን በዐዋጁ መሠረት ቦርዱ ከመገናኛ ብዙ`ኃን ባለሥልጣን ጋር በመሆን ለሣምንታት ሲያስተባብር እንደነበር ገልጸው፤ የሰዓት ድልድሉ ፖለቲካ ፓርቲዎች ፕሮግራማቸውንና ፖሊሲዎቻቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ የግል ዕጩዎችም አማራጭ ሀሳባቻቸውን እንዲያጋሩና የምርጫ ቅስቀሳ እንዲያደርጉ፣ ከመራጩ ጋር እንዲተዋወቁ ዕድል የሚሰጣቸው መሆኑን ተናግዋል። ይፋ የተደረገው ነፃ የዓየር ሰዓትን የተመዘገቡ 46 ፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች በኃላፊነት ስሜት እንዲጠቀሙበት በአፅንዖት አሳስበዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ ማካሄድ ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ያዘጋጀው የክርክር መድረክ የቦርዱን ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉን ጨምሮ አምስቱም የቦርድ ሥራ አመራር አባላት በተገኙበት በይፋ ተጀመረ። መድረኩን በንግግር የከፈቱት ሜላትወርቅ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ቦርዱ ይኽን የክርክር መድረክ ሲያዘጋጅ ፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ፣ ገለልተኛና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ፖሊሲዎቻቸውንና ፕሮግራሞቻቸውን የሚያስተዋውቁበት መድረክን መፍጠር ብቻ ሣይሆን፤ መራጩም በዛው ልክ አማራጭ የፖሊሲ ሃሳቦችን የመስማት ዕድል ኖሮት እንዲወሥን ለማስቻል በማሰብ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ይኽ የክርክር መድረክ በመካሄድ ላይ ያለው የመራጮች ምዝገባ ላይ የበለጠ መነቃቃትን እንደሚፈጥር ተናግረው፤ መራጮችም በማንዋልና በዲጂታል አማራጭ በመካሄድ ላይ ያለው የመራጮች ምዝገባ ከመጠናቀቁ በፊት ተመዝግበው ካርድ እንዲወስዱ አስታውሰዋል።

Share this post

ቦርዱ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎች በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የሚኖራቸውን ቅደም ተከተል ለመወሠን የሚያስችለውን የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት በይፋ አስጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎች በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የሚኖራቸውን ቅደም ተከተል ለመወሠን የሚያስችለውን የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት ዛሬ መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም.

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚደረግባቸው አካባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት መጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም. 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚደረግባቸው አካባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያየ። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉን ጨምሮ አምስቱም የቦርድ ሥራ አመራር አባላት በተገኙበት በተደረገው ውይይት ላይ ቦርዱ ቀደም ሲል ከፖለቲካ ፓርቲዎች የሰበሰበው ሥጋት አለባቸው ብለው የለዩዋቸው አካባቢዎች ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፤ በውይይቱ ከተነሡ ተጨማሪ አጀንዳዎች ውስጥም በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ ያለ የፀጥታ ሥጋትና በነፃነት የምረጡኝ ቅስቀሳ ያማድረግ ሁኔታ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ያለምንም ተፅዕኖ ሥራቸውን ማከናወን፣ የፖለቲካ ምኅዳርን በተመለከተ የተቸገሩ መሆኑ ይጠቀሳሉ።

Share this post

ስለ ዲጂታል መራጮች ምዝገባ የተሰጠ ማብራሪያ

የመጪውን ምርጫ ግልጽ፣ ተዓማኒ እና ቀልጣፋ ለማድረግ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ አንዱ የሪፎርም አካል መሆኑ ይታወቃል።

በዚህም መሠረት የዲጂታል መራጮች ምዝገባ ሥርዓትን በሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅቶች ተጠናቀው ወደ ተግባር ተገብቷል። ይሁን እንጂ፣ በዛሬው ዕለት የተጀመረው የዲጂታል መራጮች ምዝገባ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ሳይሆን በተመረጡ ጣቢያዎች ላይ ብቻ የሚከናወን መሆኑን በድጋሚ ለሕዝብ ግልጽ ማድረግ እንወዳለን።

መራጮች ሊገነዘቧቸው የሚገቡ ዋና ዋና ነጥቦች፦

የዲጂታል ምዝገባው የሚካሄደው አስቀድመው ለዚህ ተግባር በተለዩ ውስን ጣቢያዎች ብቻ ነው።

በዲጂታል ምዝገባ በማይካሄድባቸው ሌሎች ጣቢያዎች ሁሉ፣ የመራጮች ምዝገባ እንደተለመደው በመዝገብ (በማኑዋል) የሚቀጥል ይሆናል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያቀረበው “ምርጫችን ነው - ሀገር ያለኛ” የተሰኘ ኅብረ ዝማሬ በይፋ አስመረቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ሂደት የዜጎችን ተሣትፎን ለማበረታታት “ምርጫችን ነው -ሀገረ ያለኛ” የተሰኘ አዲስ የምርጫ ኅብረ ዝማሬ ዛሬ የካቲት 25 ቀን 2018 ዓ.ም. በይፋ አስመረቀ። የኅብረ ዝማሬው ዐላማ በዋናነት በምርጫ ሂደት ውስጥ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች ያላቸውን ተሣትፎ ማሳደግ፣ ዜጎች በምርጫው ወቅት መብትና ግዴታቸውን ተገንዝበው በንቃት እንዲሣተፉ ማነሳሳት እና ማበረታታት እንዲሁም የልዩ ልዩ ድምፆች ኅብራዊነት ያለውን የጋራ ጥንካሬ በማሳየት፣ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ አሣታፊነትንና አንድነትን ማጎልበት ነው።

የኅብረ ዝማሬውን ይፋ ማድረጊያ መድረክ በንግግር የከፈቱት ሜላትወርቅ፤ ቦርዱ ቀደም ሲል በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫም “የሀገር ካስማ” የሚል ኅብረ ዝማሬ ይፋ ማድረጉን አስታውሰው፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫም እንዲሁ “ምርጫችን ነው -ሀገረ ያለኛ” የሚል አዲስ ኅብረ ዝማሬን አካታች ተሣትፎን ለማበረታታት በማሰብ ይፋ እንዳደረገ ተናግረዋል።

Share this post

ቦርዱ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት ይፋ ባደረገበት መድረክ ላይ ፓርቲዎች የምርጫ ሥነ-ምግባር ደንብ ፈረሙ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባሳለፍነው ሣምንት መጠናቀቂያ ባዘጋጀው መድረክ ላይ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ሥነ-ምግባር ደንብ ፈረሙ። ፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት ተወካዮች እንዲሁም መገናኛ ብዙ`ኃን በተገኙበት፤ 48 ፖለቲካ ፓርቲዎች ለምርጫ የሚወዳደሩባቸውን ምልክቶች ይፋ ለማድረግ የተዘጋጀውን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ቦርዱ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት ይፋ እስከሚያደርግበት ጊዜ ድረስ በነበረው የቅድመ-ምርጫ ተግባራቱ ምን ሲያከናውን እንደነበር ማብራሪያ ሰጥተዋል። የሥነ-ምግባር ደንቡን አስፈላጊነት አስመልክቶ ባደረጉት ንግግርም ምርጫ ነፃ፣ ሰላማዊና ፍትሐዊ ሆኖ የሚከናወነው ሁሉም ፓርቲ ሕግን አክብሮ ኃላፊነቱን ሲወጣ እንደሆነ፤ የምርጫው ስኬትም የሚረጋገጠውም ቦርዱ ለብቻው በሚያደርገው ጥረት ሣይሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት ዕኩል ኃላፊነቱን መወጣት ሲችል እንደሆነ በአጽንዖት ተናግረዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዋና አሠልጣኞች ሥልጠና መስጠት ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመሥክ አሠልጣኞችን በተዋረድ ለሚያሠለጥኑ ዋና አሠልጣኞች ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሥልጠና መስጠት ጀመረ። በትላንትናው ዕለት የካቲት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. የጀመረውንና በዛሬው ዕለት የሚጠናቀቀውን ሥልጠና የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በመክፈቻ ንግግራቸው፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊ እና ገለልተኛ እንዲሆን የምርጫ አስፈጻሚዎች ሚና የማይተካ በመሆኑ፤ ብቁ እና በሕግ መሠረት የሚሠሩ ምርጫ አስፈጻሚዎችን ለማብቃት የዋና አሠልጣኞች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን፤ ዋና አሠልጣኞቹ በሁለቱ ቀናት የሚያገኙትን ሥልጠና በትኩረትና በኃላፊነት ስሜት ለመሥክ አሠልጣኞች ማስተላለፍ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።

Share this post

ቦርዱ ሐሰተኛና አደናጋሪ ምርጫ ነክ መረጃዎችን ለመከላከል የሚያስችለውን ብሔራዊ ትብብር ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በያዝነው ሣምንት በምርጫ እና በድኅረ ምርጫ ወቅት ሊፈጠሩ የሚችሉ ምርጫ ነክ ሐሰተኛና አደናጋሪ መረጃዎችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የሚያስችለውን የብሔራዊ ትብብር ስምምነት ይፋ አደረገ። የይፋ ማድረጊያው መድረኩን የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በንግግር የከፈቱት ሲሆን፤ በንግግራቸውም የትብብር ማዕቀፉ ቦርዱ መጪው ምርጫ ነፃ እና ተዓማኒ እንዲሆን ምርጫ ነክ መረጃዎች ተዛብተው እና አሳሳች ሆነው ለኀብረተሰቡ እንዳይቀርቡና 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተዓማኒነት ተጠብቆ እንዲከናወን ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራበት ነው ብለዋል።

Share this post