ቦርዱ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመምረጥ የሚሳተፉበትን ምቹ መደላድል ለመፍጠር ያለመ ውይይት ከተቋማቱ አመራሮች ጋር አደረገ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ከትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች ጋር የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የመራጮች ምዝገባ እና ድምጽ አሰጣጥን በሚመለከት ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ውይይት አደረገ፡፡
ውይይቱ የተካሄደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ፣ የዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚዳንቶች፣ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እና የትምህርት ሚኒስቴር ተወካይ በተገኙበት ነው፡፡
የውይይቱ ዓላማ ከምርጫ ክልላቸው ርቀው በዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች ልዩ የምርጫ ጣቢያ ተዘጋጅቶላቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ያለመ ነው፡፡