ቦርዱ በምርጫ መታዘብ ለሚሳተፉ የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች የበይነ-መረብ ምዝገባ እና መረጃ አያያዝ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ-ግብር አካሄደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለሚታዘቡ የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች በበይነ-መረብ አማካኝነት ምዝገባ እንዲያደርጉ እና መረጃ እንዲያደራጁ የሚያስችላቸውን የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ-ግብር ከጥቅምት 25-26 ቀን 2018 ዓ.ም. አካሄደ።
በበይነ-መረብ አማካኝነት የሚደረገው ምዝገባ እና የመረጃ አያያዝ ቀድሞ በተለምዷዊ ስርዓት ይከናወን የነበረውን አሰራር በዘመናዊ ስርዓት የቀየረ ነው። የግንዛቤ ማስጨበጫው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በበለጸገው የበይነ-መረብ መመዝገቢያ እና መረጃ መያዣው ላይ የራሳቸውን ግብዓት እንዲጨምሩበትም ያለመ ነው።
በበይነ-መረብ የሚደረገው ምዝገባ እና መረጃ አያያዝ፤ የመረጃዎችን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ እንደሚረዳ፣ በተገቢው ለመሰነድ እና የመረጃ ትንተና ለማዘጋጀት በእጅጉ ጠቃሚ እንደሆነ በመርሀግብሩ ላይ ተጠቅሷል።