የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሥነ-ዜጋ እና ለመራጮች ትምህርት ክፍል ባለሙያዎቹ የዐቅም ግንባታ ሥልጠና ሰጠ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ በ2018 የሚያስፈጽመው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ እያከናወናቸው ከሚገኙ በርካታ ተግባራት ውስጥ የቦርዱን ባለሞያዎች ዐቅም የሚያጎለብቱ ሥልጠናዎችን መስጠት ይጠቀሳል። ቦርዱ ነሐሴ 28-29 ቀን 2017 ዓ.ም. ለዋናው መሥሪያ ቤትና ለቅርንጫፍ ጽ/ቤቶቹ የሥነ-ዜጋ እና የመራጮች ትምህረት ሥራ ክፍል ባለሞያዎቹ ሥልጠና ሰጠ። የሥልጠናውን የመክፈቻ ንግግር የቦርድ አመራር አባል የሆኑት ተክሊት ይመስል ያደረጉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም የሥልጣን ባለቤት ሕዝብ መሆኑን አስታውሰው የመራጮች ትምህርት መስጠቱም፤ የሥልጣን ባለቤት የሆነው ሕዝብ አስፈላጊው ግንዛቤ ኖሮት እንዲመርጥ እንደሚያስችለው ተናግረዋል። ይኽም ሲሆን በሥልጠናዎቹ አካታች መሆን መሠረታዊ ነገርና የግድ የሚል እንደሆነ አስገንዝበዋል።