የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህጻናት ፓርላማ ምስረታ ሥልጠና እና ሙያዊ ድጋፍ ሰጠ!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 102 መሰረት ምርጫን የማስፈጸም ሥልጣን የተጣለበት ገለልተኛ ተቋም ነው፡፡ በመሆኑም ዜጎች በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እና በምርጫ ሂደት ዙሪያ ግንዛቤን ያገኙ ዘንድ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ በዚህም መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህጻናት ፓርላማ ባካሄደው የምስረታ እና የሥራ አስፈጻሚዎች ምርጫ ላይ በቦርዱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኩል የምርጫ ኦፕሬሽን እና የሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍሎች ባለሙያዎች በምርጫ ሂደት እና በዴሞክራያዊ መብት ልምምድ ዙሪያ ሥልጠና ሰጥተዋል።