Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ሥነ-ዘዴውን የተመለከተ ዐውደ-ጥናት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አማካሪ ድርጅት ቀጥሮ ያሠራው የቦርዱን የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ሥነ-ዘዴ የገመገመ መነሻ ጥናት መጠናቀቁን ተከትሎ ግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም. ባካሄደው ዐዋደ-ጥናት፤ የጥናቱን ሂደትና ግኝት እንዲሁም ጥናቱን ተከትሎ የተሰጠውን ምክረ-ሃሳብ በአማካሪ ድርጅቱ ባለሞያዎች አማካኝነት ዐውደ ጥናቱ ላይ ተሣታፊ ለነበሩት የቦርዱ አመራሮች፣ ለሚመለከታቸው የቦርዱ ሥራ ክፍሎችና ባለድርሻ አካላት አቅርቧል።

Share this post

የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሁለተኛ ዙር የምርጫ ጣቢያዎችን በዲጂታል ሲስተም የመመዝገብ ሥራ ማከናወን ጀመረ

የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንደ አዲስ ከተቋቋመበት 2011 ዓ.ም. አንሥቶ አንድ ሀገራዊ ምርጫ እና ሦስት ሕዝብ ውሣኔዎችን ማስፈጸሙ ይታወቃል። ቦርዱ በቀጣይም የ7ኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ ለማከናወን የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች አጋርነት መድረክ አስፈላጊነት ላይ ውይይት ተካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች (ሲ.ማ.ድ) ጋር የሚኖር የአጋርነት መድረክ አስፈላጊነት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ። ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ምርጫ ቦርድ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምርጫን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ለሚኖራቸው ተሣትፎ ዕውቅና ከመስጠት አንሥቶ አብሮ እስከመሥራት የደረሰ ግንኙነት እንዳለው አስታውሰው፤ ይኽም ሲሆን ሚናን በመለየት ተባብሮ መሥራቱ የምርጫን ነፃና ገለልተኛ እንዲሁም ዲሞክራሲያዊነቱን በማረጋገጥ ረገድ ከፍ ያለ አስተዋፅዖ ያለው በመሆኑ እንደሆነ ተናግረዋል። በዚኽም መድረክ ላይ ማኅበራቱ በምርጫ ትምህርትም ላይ ባላቸውም ተሣትፎ ይሁን እንደታዛቢ በሚኖራቸው ኃላፊነት መሻሻል የሚገባቸውን እየለዩ መሄድና የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።

Share this post

ቦርዱ የፓለቲካ ፓርቲዎችን አቅም ለመገንባት የፓለቲከኞችን የምርጫ ክህሎት ለማጎልበት ሥልጠና መስጠት ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከኔዘርላንድ የመድብለ ፓርቲ የዲሞክራሲ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከተለያዩ የፓለቲካ ፓርቲዎች ለተውጣጡ ፓለቲከኞች በምርጫ ክርክር ክህሎት ላይ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

የሥልጠናው ዋንኛ ዓላማ ፓለቲከኞች ለመራጩ የሚያቀርቡት ማኒፌስቶ (ፓሊሲዎችና ፕሮግራሞች) የህዝብ ቅቡልነት እንዲያገኙ የፓለቲከኞች የምርጫ ክርክር ክህሎትን ማሳደግ ላይ ያተኮረ ነው።

በምርጫ ክርክር አማካኝነት ተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች ለመራጩ ህዝብ በሚሰጡት አማራጭ የፓሊሲ አማራጮች ምክንያት መራጮች ዕውቀት ላይ ተመስርተው የሚበጃቸውን እንዲመርጡ ከማስቻሉ ባሻገር የዲሞክራሲ ተሳትፎ ባህልን ይጎለብታል።

Share this post

ዓሲምባ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲን በተመለከተ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ ውሳኔ

እነ ዶሪ አስገዶም ዓሲምባ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ/ዓዴፓ/ በሚል ስያሜ በ26/2/2012 ዓ.ም የክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ ህጋዊ የእውቅና ጥያቄ ለቦርዱ አቅርበው በምዝገባ ሂደት ላይ የነበሩ ሲሆን፤ የፓርቲው ህጋዊ የእውቅና ፈቃድ ሂደት በአገራችን በተከሰተው ጦርነት ምክንያት ተቋርጦ ቆይቶ በኋላም እነ ሐጎስ ወልዱ በቁጥር ዓዴ-0027/15 በቀን 25/07/2015 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ተቋርጦ የነበረው ሂደት እንዲቀጥል በማለት አመልክተዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በድጋሚ በቁጥር ዓዴ-0032/15 በቀን 16/09/2015 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ጊዜያዊ የእውቅና ፈቃድ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት ለመስጠት ፈቃደኛ ለሆኑ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስልጠና ሰጠ።

የቦርዱ የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት የስራ ክፍል የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርትን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ ከተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በጋራ እየሰራ ይገኛል።

ትምህርቱን በመላው ሀገሪቱ በስፋት ተደራሽ ለማድረግ የበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት የሚሰጡ ወጣቶችን ከየክልሉ በመመልመል በየአካባቢያቸው ለማሰማራት እቅድ የያዘ ሲሆን በቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኩል ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለተውጣጡ 25 የሁለተኛ እና ሦስተኛ ዓመት ተማሪዎች ከሚያዝያ 4 እስከ 5 /2017 ዓ.ም የቆየ የሁለት ቀናት የመጀመሪያ ዙር ስልጠና ሰጥቷል።

Share this post