Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ለሚካሄደው ሕዝበ ውሣኔ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት በቦርዱ ፈቃድ የተሰጣቸው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 124 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት መራጮች በቂ ምርጫ ነክ ግንዛቤ የሚያገኙበትን ሥልት በመቀየስና የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ይሰጣል። ከዚህም በተጨማሪ ቦርዱ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት መስጠት እንዲችሉ ሕጋዊ ሰውነት ላላቸው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና የትምህርት ተቋማት፤ የማስተማር ፈቃድ ይሰጣል። በዚህም መሠረት ቦርዱ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ማለትም በጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዲዮ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም ቡርጂ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ እና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ላይ የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ የመራጮች ትምህርት ለመስጠት ለሚፈልጉ የሲቪል ማኅበረሰብ ተቋማት ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፤ በጥሪውም መሠረት ቦርዱ መሥፈርቱን አሟልተው ለቀረቡ 16 የመጀመሪያ ዙር የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ሰጥቷል።

Share this post

በሕዝበ ውሳኔ ጥያቄ ዙርያ ክርክር/ውይይት ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው አካላት የተደረገ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ማለትም በጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዲዮ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም ቡርጂ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ እና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ላይ የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ እንደሆነ ይታወቃል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የምርጫ ቦርዱ በሕዝብ ውሣኔው ላይ በሚነሡ የተለያዩ ሃሳቦች ላይ የሚደረገውን ክርክር ለማስተባበር ይፈልጋል። በመሆኑም ቦርዱ በዚሁ ጉዳይ ላይ ፍላጎት ያላችሁ ተቋማት እና መገናኛ ብዙኃንን በተናጠል ወይም በጋራ በመሆን ክርክር የማዘጋጀት ዝርዝር የፍላጎት መግለጫ (Expression of interest) እንድታቀርቡ ጥሪ ያቀርባል።

ማንኛውም በህዝበ ውሳኔ ዙርያ ክርክር ወይም ውይይት ለማዘጋጀት የሚያስብ ተቋም የሚመለከቱትን ዋና ዋና ነገሮችን የያዘ የፍላጎት መግለጫ ሰነድ ሊያቀርብ ይገባል።

በሕዝበ ውሳኔ ጥያቄ ላይ በሚደረግ ክርክርና ውይይት ለመሳተፍ ፍላጎት ላላቸው የተደረገ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ማለትም በጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዲዮ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም ቡርጂ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ እና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ላይ የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ እንደሆነ ይታወቃል። በዚህ መሰረት የመራጮች የግል ውሳኔ በመረጃ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን የሚያስችል በቂ መረጃ እና ሀሳብ እንዲያገኙ ለማድረግ ቦርዱ በህዝበ ውሳኔው አማራጮች ላይ ሃሳቦች እና አስተያየቶች ወደ ህዝብ የሚቀርብባቸውን የክርክር፣ የውይይት፣ እና የምከክር መድረኮችን በማመቻቸት ላይ ይገኛል።

በሕዝበ ውሳኔ ጥያቄ ላይ በሚደረግ ክርክርና ውይይት ለመሳተፍ ፍላጎት ላላቸው የተደረገ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ማለትም በጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዲዮ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም ቡርጂ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ እና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ላይ የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ እንደሆነ ይታወቃል። በዚህ መሰረት የመራጮች የግል ውሳኔ በመረጃ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን የሚያስችል በቂ መረጃ እና ሀሳብ እንዲያገኙ ለማድረግ ቦርዱ በህዝበ ውሳኔው አማራጮች ላይ ሃሳቦች እና አስተያየቶች ወደ ህዝብ የሚቀርብባቸውን የክርክር፣ የውይይት፣ እና የምከክር መድረኮችን በማመቻቸት ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ላይ ያሳለፈውን የመሠረዝ ውሣኔ አነሣ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄን (ጉሕዴን) በዐዋጅ 1162/2011 እና ይህንኑ ዐዋጅ ተግባራዊ ለማድረግ ቦርዱ ባወጣው መመሪያ ቁጥር ሦስት መሠረት በዳግም ምዝገባ ሂደት ውስጥ ማለፍ ከነበረባቸው ፓርቲዎች መካከል አንዱ ስለነበር፤ ፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔ በማድረግ መተዳደሪያ ደንቡን አሻሽሎ እንዲያቀርብ በወቅቱ መመሪያ ተሰጥቶ ነበር፡፡ ይሁንና ፓርቲው ለዳግም ምዝገባ የሚያበቃውን ሕጋዊ ቅድመ ሁኔታ በወቅቱ ባለማሟላቱ ከምዝገባ እንዲሠረዝ ቦርዱ ወሠነ፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥርዓተ ፆታ አካታችነትን አስመልክቶ ለቦርዱ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እና ባለሞያዎች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥቅምት 21 እና 22 ቀን 2015 ዓ.ም. የቦርዱን ተግባራት የሥርዓተ ፆታ እና አካታችነትን ባማከለ መልኩ እንዲፈጸም የሚያስችል ሥልጠና ሰጠ። ይህ የቦርዱን የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እንዲሁም ባለሞያዎች ዐቅም ለመገንባት ታስበው በመሰጠት ላይ ካሉት ሥልጠናዎች መካከል አንዱ የሆነው ሥልጠና ዐላማው፤ የተሣታፊዎችን የሥርዓተ ፆታ ግንዛቤ ከማሳደግም ባለፈ በፖሊሲ ቀረጻ እንዲሁም በዕቅድ አወጣጥ እና አተገባበር ላይ ታሳቢ መደረግ ስለሚኖርባቸው የሥርዓተ ፆታና አካታችነት አሠራሮች ተለይተው እንዲታወቁ ማድረግ ሲሆን፤ በተጨማሪም የሥራ ክፍሎቹን የዕለት ተለት ሥራዎቻቸውን እንዴት ሥርዓተ ፆታና አካታችነትን ታሳቢ ባደረገ መልኩ መፈጸም እንዳለባቸው ክኅሎት ማስጨበጥ ነው።

Share this post

በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ መዘገብ ለምትፈልጉ የመገናኛ ብዙኃን የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖሊቲካ ፓርቲዎች እና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 እና ቦርዱን ባቋቋመው የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 1133/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት፣ ምርጫውን ለመዘገብ ለሚፈልጉ የመገናኛ ብዙኃን ፈቃድ ለመስጠት እና ለመከታተል የሚያስችለውን መመሪያ አርቅቆ፣ የመገናኛ ብዙኃን እና የጋዜጠኞች የምርጫ አዘጋገብ የሥነ ምግባር እና አሠራር መመሪያ ቁጥር 02 /2013 አፅድቋል።

Share this post

ጀማሪ ባለሙያዎችን ለመቅጠር የወጣ ክፍት ሥራ ቦታ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሥሩ ለሚገኙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ጀማሪ ባለሙያዎችን /Intern/ በኮንትራት ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡

በዚሁም መሠረት

- በህግ፣ በኮምፒውተር ሳይንስ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በኮምፒውተር ኢንጅነሪንግ፣ በሶሺዎሎጂ፣ ሶሻል ወርክ፣ በህዝብ አስተዳደር፣ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን፣ በሰው ኃብት አስተዳደር፣ በቢዝነስ ሊደርሺፕ፣ በማርኬቲንግ ማኔጅመንት፣ በአካውንቲንግና ፋይናንስ፣ በኢኮኖሚክስ፣ በግዢ እና ንብረት አስተዳደር፣ በጋዜጠኝነት እና ስነጽሁፍ፣ በግራፊክስ ዲዛይን፣ በፖለቲካል ሳይንስ እና አለምአቀፍ ግንኙነት እንዲሁም ተያያዥ የትምህርት ዘርፎች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው/ያላት

- አማካይ የመመረቂያ ውጤታቸው 3.5 እና ከዛ በላይ የሆነ፤

- ጥሩ የሆነ የአማርኛ እና የእንግሊዘኛ ቋንቋን ክህሎት (መናገር፣ መጻፍ እና ማንበብ) ያለው/ያላት፤

በደ/ብ/ብ/ህዝቦች ክልል 6 ዞኖች እና 5 ልዩ ወረዳዎች ህዝበ ውሳኔ ዙሪያ የመራጮች ትምህርት መሰጠት ለሚፈልጉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ስር የሚገኙ 6 ዞኖች ማለትም የጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ጌዲዮ፣ ኮንሶና ደቡብ ኦሞ ዞኖች እና 5 ልዩ ወረዳዎች ማለትም የቡርጂ፣ አማሮ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ ልዩ ልዩ ወረዳዎች ህዝበ ውሳኔ ያካሂዳል ፡፡

ዜጎች ህዝበ ውሳኔው ላይ ያላቸውን ትርጉም ያለው ተሳትፎ ለማረጋጋጥ ብሎም ተአማኒነትን ያተረፈ ሰላማዊ ህዝበ ውሳኔ ለማድረግ የመራጮች ትምህርት አስፈላጊነት እሙን ነው፡፡ ይህንን አላማ ለማሳካትም የሲቪል ማህበረሰብ ተሳትፎ ትልቅ ስፍራ ይይዛል፡፡

Share this post

ለደ/ብ/ብ/ሕ/ክልል ለሚያካሄደው የሕዝበ ውሳኔ የምርጫ አስፈፃሚዎችን በጊዜያዊነት ለመቅጠር የወጣ ክፍት ሥራ ቦታ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልል በ6 ዞን እና በ5 ልዩ ወረዳዎች ላይ የሕዝበ ውሳኔ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ ሕዝበ ውሳኔውን የሚያስፈጽሙ ሰራተኞችን በጊዚያዊነት ለመቅጥር ይፈልጋል። በዚሁ መሰረት በጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዲዮ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም ቡርጂ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ እና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ውስጥ የምትኖሩ በምርጫ አስፈጻሚነት በገለልተኝነት ማገልገል የምትፈልጉ እና ከፓርቲ አባልነት ነጻ የሆናችሁ ከዚህ በታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ከጥቅምት 12-20 ቀን 2015 ዓ.ም ብቻ እንድታመለከቱ ቦርዱ ይጠይቃል።

ወደ ገፁ ለመግባት እዚህ ላይ ይጫኑ

የምልመላ መስፈርት፡