የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ቅንጅት) መሥራች አባላት ስም ዝርዝርን እንዲያጣራ ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ጥያቄ አቀረበ
የካቲት 27 ቀን 2012 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቀድሞ አዋጅ ተመዝግበው የሚገኙ የፓለቲካ ፓርቲዎች በአዲሱ ህግ ላይ ተቀመጡትን መሥፈርቶች እንዲያሟሉ መጠየቁ ይታወሳል። በዚህም መሠረት ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ በአዲሱ አዋጅ በተደነገገው መሠረት 7,214 (ሰባት ሺህ ሁለት መቶ አስራ አራት) ተጨማሪ መሥራች የፓርቲ አባላትን አስፈርሞ እስከ መጋቢት 3 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ እንዲያቀርብ ተገልጾለት ነበር። ፓርቲው ጥር 26 ቀን 2012 ዓ.ም. ከ8 ክልሎች የተሰበሰበ የመሥራች አባላት ፊርማ የያዘ ሰነድ ለቦርዱ አቀርቧል። በመሆኑም የቀረበው ሰነድ ላይ የሚከተሉትን ቦርዱ አስተውሏል፡፡
