Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን ለሚያካሄደው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ የምርጫ አስፈጻሚዎች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በወላይታ ዞን የሚያካሄደው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ላይ ለሚሣተፉ በየደረጃው ለሚገኙ የምርጫ አስፈጻሚዎች ሥልጠና ሰጠ። ከግንቦት 16 ቀን እስከ ግንቦት 21 ቀን 2015 ዓ.ም በተሰጠው ሥልጠናም የሥራ ትውውቅ፣ የውጤት ማመሳከር፣ የማዳመርና የይፋ አደራረግ ላይ ያተኮረ ሥልጠና ለዞንና ለማዕከል አስተባባሪዎች የተሰጠ ሲሆን፤ ለመሥክ አሠልጣኞችም እንዲሁ የአሠልጣኞች ሥልጠና በሶዶ ከተማ ተሰጥቷል።

በተጨማሪም ቦርዱ በወላይታ ዞን ውስጥ በተቋቋሙ 12 ማስተባበሪያ ማዕከላት ላይ ለ3608 የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎች በሁለት ዙር ሥልጠና በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ዙር ሥልጠና ከግንቦት 23 እስከ ግንቦት 25 ቀን 2015 ዓ.ም ሲሰጥ፤ የሁለተኛ ዙር ሥልጠናም እንዲሁ ከግንቦት 26 እስከ ግንቦት 28 ቀን 2015 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን በሚካሄደው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ምርጫ የመራጮች ትምህርት ላይ ከሚሣተፉ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ውይይት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን በሚካሄደው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔን ምርጫ ላይ የመራጮች ትምህርት ተደራሽነት ላይ ለሚሠሩና በቦርዱ የገንዘብ ድጋፍ ከተደረገላቸው ሰባት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ግንቦት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. ውይይት አካሄደ። ዐላማውን ድጋፍ የሚደረግላቸው ድርጅቶች የሚደረግላቸውን ድጋፍ በምን አግባብ መጠቀም እንዳለባቸው፤ እንዲሁም ከዕቅድ አንጻር አፈጻጸማቸውና የፋይናንስ ሪፖርት አቀራረባቸውን አስመልክቶ ግልጽ መግባባት ላይ ለመድረስ ያደረገውን ውይይት በንግግር የከፈቱት የቦርድ አመራር አባል የሆኑት ዶ/ር አበራ ደገፋ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ቦርዱ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም.

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል በሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሓ.ት) ላይ ያስተላለፈውን የፓርቲውን ሕጋዊ ሰውነት ሥረዛ ፓርቲው ይነሣልኝ ሲል ያቀረበውን ጥያቄ ቦርዱ ውድቅ ያደረገበት ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል በሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሓ.ት) ላይ ያስተላለፈውን የፓርቲውን ሕጋዊ ሰውነት ሥረዛ ፓርቲው ይነሣልኝ ሲል ያቀረበውን ጥያቄ ቦርዱ ውድቅ ያደረገበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የብሔራዊ ባይቶ ዓባይ ትግራይ (ባይቶና) ፓርቲው አደራጅ ኮሚቴ ዐዋጁን መሠረት በማድረግ የመሥራች ጉባዔውን እንዲያከናውን መወሠኑን ያሳወቀበት ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የብሔራዊ ባይቶ ዓባይ ትግራይ (ባይቶና) ፓርቲው አደራጅ ኮሚቴ ዐዋጁን መሠረት በማድረግ የመሥራች ጉባዔውን እንዲያከናውን መወሠኑን ያሳወቀበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የሳልሳይ ወያነ ትግራይ ፓርቲ አደራጅ ኮሚቴ ዐዋጁን መሠረት በማድረግ የመሥራች ጉባዔውን እንዲያከናውን መወሠኑን ያሳወቀበት ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የሳልሳይ ወያነ ትግራይ ፓርቲ አደራጅ ኮሚቴ ዐዋጁን መሠረት በማድረግ የመሥራች ጉባዔውን እንዲያከናውን መወሠኑን ያሳወቀበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በዎላይታ ዞን የድጋሚ ህዝብ ውሳኔ ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እያከናወነ ነው።

በዚሁ መሠረት በዎላይታ ዞን ስር በሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ ህዝበ ውሳኔ የሚያስፈጽሙ ሠራተኞችን በጊዜያዊነት ለመቅጠር ይፈልጋል። በመሆኑም የዎላይታ አካባቢ ነዋሪ የሆናችሁ፣ በምርጫ አስፈጻሚነት በገለልተኝነት ማገልገል የምትፈልጉ እና ከፓርቲ አባልነት ነፃ የሆናችሁ አመልካቾች ከግንቦት 3 እስከ ግንቦት 10 ቀን 2015 ዓ.ም ብቻ እንድታመለከቱ ቦርዱ ያሳውቃል።

የምልመላ መሥፈርት፡-

• ዕድሜው/ዋ ከ18 ዓመት በላይ የሆነ/ች፣

• የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ች፣

• የትምህርት ዝግጅት፦12ኛ ክፍል ያጠናቀቀ/ች እና ከዚያ በላይ የሆነ/ች፣

• የሥራ ቦታ፦ በዎላይታ ዞን ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ቀበሌ እና ምርጫ ጣቢያዎች፣

• የስራ ቆይታ ፦ ከ8 እስከ 10 ቀን

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን የሚካሄደውን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔን ምርጫ በተመለከተ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና ከኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጋር ምክክር አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን የሚደረገውን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ምርጫ አስመልክቶ በመራጮች ትምህርትና በምርጫ መታዘብ ላይ ከተሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እንዲሁም በሰብዓዊ መብት ክትትል ተግባራት ላይ ከተሠማራው ከኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጋር ሚያዚያ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. ውይይት አካሄደ። የውይይት መድረኩ የቦርድ አመራር አባል የሆኑት ብዙወርቅ ከተተ ባደረጉት ንግግር የተከፈተ ሲሆን፤ በንግግራቸውም የድጋሚ ምርጫ ማካሄድ ያስፈለገበት ዋና ዋና ምክንያቶች አብራርተዋል። በተጨማሪም የመራጮች ትምህርት በሚሰጥበት ወቅት ምን ምን ጉዳዮች መካተት እንዳለባቸው እና ልዩ ድጋፍ የሚሹ የማኅበረሰቡን ክፍሎች ተደራሽ ሊደረጉ የሚችሉበትን አግባብነትና አማራጮች አስረድተዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልል በሚገኘው የዎላይታ ዞን ላይ የሚያካሄደው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ የትግበራ አፈጻጸም ዝርዝር ዕቅድ ማሳያ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልል በሚገኘው የዎላይታ ዞን ላይ የሚያካሄደው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ የትግበራ አፈጻጸም ዝርዝር ዕቅድ ማሳያ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳ

wolita election time table

 

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን የሚደረገውን የድጋሜ የሕዝበ ውሣኔ ምርጫ አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን የሚደረገውን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ምርጫ አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትላንትናው ዕለት ሚያዚያ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. ውይይት አካሄደ። የፌዴሬሽን ምክር ቤትና የሕዝብ ተወካዩች ቋሚ ኮሚቴ ተወካዩች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች፣ የዞኑ አመራሮችና የፀጥታ አካላት እንዲሁም የፌደራል ፖሊስና የፍትሕ ሚኒስቴር ተወካዮች የተገኙበትን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም የመድረኩ ዋና ዐላማ በወላይታ ዞን የተደረገው ሕዝበ ውሣኔ ላይ ቀደም ሲል ያጋጠሙ የሕግ ጥሠቶች በድጋሚ እንዳይፈጠሩ አስቻይ ሁኔታዎችን በጋራ ለመፍጠር ታሳቢ እንዳደረገና ይህንንም ለማድረግ የመድረኩ ተሣታፊ የሆኑት ባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ እንደሆነ በማሰብ ጭምር እንደሆነ ተናግረዋል።

Share this post