Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 08 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 08 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:00 ሰዓት ባንቢስ ሱፐር ማርኬት ዐለፍ ብሎ በሚገኘው ዲ-ሊኦፖል ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። 

•በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣ 
•የቦርዱን ልዩ የዘገባ ባጅ ፊት ለፊት ማንጠልጠል
•ከአንድ ሚዲያ ሁለት ባለሞያዎች (የፎቶ/የቪዲዮ ባለሙያን ጨምሮ) ብቻ መሣተፍ ይችላሉ። 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሰኔ 08 ቀን 2013 ዓ.ም

Share this post

ለፓለቲካ ፓርቲዎች እና ለግል እጩዎች በሙሉ

የድምጽ መስጫ ቀን ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሆነ ይታወቃል። በመሆኑም የድምጽ መስጫ ቀን በምርጫ ጣቢያ በመገኘት የሚታዘቡ የፓርቲ ወኪሎቻችሁን እውቅና ለማሰጠት እና ባጅ ለማግኘት በምትወዳደሩበት ምርጫ ክልል ቢሮ በመሄድ ዝርዝራቸውን እንድታስገቡ እናሳውቃለን። ዝርዝር ማስገቢያው ቅጽ እና ቃለመሃላ ፎርም ከዚህ ማስታወቂያ ስር ተያይዟል።

የእጩ ወኪልነት መስፈርቶች

• በእጩ ወኪልነት የሚቀርብ/የምትቀርብ ማንኛውም ሰው የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት አለበት/አለባት።

1. ኢትዮጵያዊ ዜጋ የሆነ/ች፣

2. እድሜ 21 ዓመት እና ከዚያ በላይ የሆነ/ች፣

3. የመምረጥ እና መመረጥ መብቱ/ቷ በሕግ ያልተገደበ፣

4. የታወቀ ብልሹ ስነ-ምግባር የሌለበት/ባት፣

5. ማንበብ እና መፃፍ የሚችል/የምትችል እና

6. በእጩ ተወዳዳሪነት ያልተመዘገበ/ች መሆን አለበት/ባት፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 3 ቀን 2013 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የሚከተሉትን ዋና ዋና ውሳኔዎች አሳልፏል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 02 ቀን 2013 ዓ.ም ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር ካከናወነ በኋላ ባደረገው ስብሰባ ከ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ ጋር የተያያዙ ውሳኔ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል።

1. 6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን አስቀድሞ እንደተገለጸው በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ በእለቱ ድምጽ መስጠት የማይቻልባቸው አካባቢዎች ድምጽ አሰጣጥ ጷግሜ 01 ቀን 2013 ዓ.ም ይከናወናል።

እነዚህም

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሎጀስቲክስ እና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር አካሄደ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ዛሬ ሰኔ 02 ቀን 2013 ዓ.ም የምክክር መድረክ አከናውኗል። ይህ በተደጋጋሚ ከሚደረጉ የምክክር መድረኮች አንዱ የሆነው ከፓርቲዎች ጋር የሚደረገው ምክክር በዋናነት ቦርዱ የድምጽ መስጫ ወረቀት ህትመትን አስመልክቶ ያጋጠመውን ተግዳሮት ለፓርቲዎች ሪፓርት ያቀረበበት ነው።

የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ በሪፓርታቸው እንዳቀረቡት የእጩዎችን ቁጥር መሰረት አድርጎ በተደረገው የገንዘብ ድጋፍ ወቅት ፓርቲዎች የእጩዎች ቁጥር ላይ ባቀረቡት አቤቱታ፣ በማስከተልም በድምጽ መስጫ ወረቀት እና በውጤት ማሳወቂያ ፎርሞች መካከል የማስታረቅ ስራ ሲሰራ የተወሰኑ የምርጫ ክልሎች የድምጽ መስጫ ወረቀቶች ላይ የተለያዩ ጉድለቶች መገኘታቸውን አሳውቀዋል። በዚህም መሰረት የቦርዱ ኦፕሬሽን ክፍል ባከናወነው ኦዲት 54 የምርጫ ክልሎች ድምጽ መስጫ ወረቀቶች ድጋሚ ህትመት የሚያስፈልጋቸው ሆነው ተገኝተዋል።

Share this post

መረጃ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በክስ ሂደት ላያ ያሉ የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ አባላት በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች

  • የካ ክፍለከተማ
  • ኮልፉ ቀራኒዮ ክፍለከተማ
  • ንፋስ ስልክ ላፍቶ

እንዲሁም የተወካዮች ምክር ቤት

ምርጫ ክልል 26 እና 27 በእጩነት ለመወዳደር ጥያቄ አቅርበው እንዳልተቀበለው ይታወቃል።

በዚህም መሰረት መጀመሪያ የምርጫ ክልሎቹ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ፣ በማስከተል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ቀጥሎ ከፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእጩነት ምዝገባ ጥያቄው አግባብ አይደለም ብሎ ሲከራከር እንደነበር ይታወሳል። በዚህም መሰረት ከፍተኛው ፍርድ ቤትም የቦርዱን አሰራር አጽድቆ ነበር።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመራጮች ትምህርት ላይ ከተሠማሩ የሲቪክ ማኅበረሰብ ተቋማት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመራጮች ትምህርት ላይ ከተሠማሩ የሲቪክ ማኅበረሰብ ተቋማት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ። ውይይቱን የቦርዱ አመራር አበራ ደገፋ (ዶ/ር) በንግግር የከፈቱት ሲሆን፤ በንግግራቸውም ቦርዱ የመራጮች ትምህርት ለሚያስተምሩ 167 የሲቪክ ማኅበራት ፍቃድ የሰጠ መሆኑን ገልጸው፤ እነዚህም ፈቃድ የተሰጣቸው የሲቪክ ማኅበራት በሰጡት የመራጮች ትምህርት አማካኝነት ካርድ የወሰዱ ዜጎች ቁጥር መሻሻል ያሳየ መሆኑ፤ ለዚህም ከፍተኛ አክብሮት እንዳላቸው ተናግረዋል። ሲቪክ ማኅበራቱ በቀጣይ በሚከናወነው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ዜጎች በንቃት እንዲሣተፉና ድምፃቸውን በነፃነት ለፈለጉት ዕጩ እንዲሰጡ ማሰተማር አሰፈላጊ መሆኑን፤ በድምፅ አሰጣጥ ሂደት በመራጮች መሳሳት የሚባክን ድምፅ እንዳይኖር በመራጮች ትምህርት አሰጣጥ ላይ የተሰማሩ የሲቪክ ማህበራት ትምሀርቱን በደንብ መስጠት እንደሚኖርባቸው፤ እንዲሁም በድኅረ ምርጫ ሁኔታዎች ሰላማዊ እንዲሆን ዜጎች የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ተገቢው ትምህርትና ግንዛ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ተጨማሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች የአየር ሰአት ድልድል አደረጉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የድምጽ መስጫ ቀን ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. መሆኑን ተከትሎ ከመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ጋር በመተባበር ተጨማሪ የቅስቀሳ የአየር ሰአት ድልድል ዛሬ አከናውነዋል። በዚህም መሰረት የፓለቲካ ፓርቲዎች የምረጡኝ ዘመቻቸውን እስከ ሰኔ 09 ቀን 2013 ዓ.ም. ድረስ ማከናወን የሚችሉ ሲሆን ከሰኔ 10-13 ድረስ ምንም አይነት ቅስቀሳ የማይደረግበት የፀጥታ ጊዜ ይሆናል። የመገናኛ ብዙሃን የአየር ሰአት ድልድሉም እስከ ሰኔ 09 ድረስ የሚቆይ ነው። ፓለቲካ ፓርቲዎች ተጨማሪውን የአየር ሰአት ድልድል ሰነድ ከቦርዱ የፓለቲካ ፓርቲዎች የስራ ክፍል በግንባር በመምጣት መውሰድ ወይም media [at] nebe.org .et ኢሜይል አድራሻ ላይ ጥያቄ በማቅረብ በሶፍት ኮፒ ማግኘት ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአለም አቀፍ ሪፕብሊካን ኢንስቲቲዩት (IRI) ለአለም አቀፍ የዴሞክራቲክ ኢንስቲቲዮት (NDI) የምርጫ ታዛቢ ቡድን የምርጫ መታዘብ እውቅና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከመንግስት ግብዣ መሰረት 6ተኛው አገር አቀፍ ምርጫ በጋራ ለመታዘብ በጋራ ለሚሰሩት ለአለም አቀፍ ሪፕብሊካን ኢንስቲቲዩት (IRI) ለአለም አቀፍ ዴሞክራቲክ ኢንስቲቲዮት (NDI) የምርጫ መታዘብ እውቅናን ሰጥቷል። ቦርዱ የድርጅቶቹ የጋራ የታዛቢ ቡድን ያቀረበውን የጥናት ዘዴ በማየት እንዲሁም በአለም አቀፍ ታዛቢዎች መሰረታዊ መርህዎችን እና የታዛቢዎች አለም አቀፍ የስነምግባር ደንብ በተከተለ መልኩ እንደሚሰሩ ስምምነት ላይ በመድረስ የመታዘብ እውቅናውን የሰጠ ሲሆን በአለም አቀፉ የኮቪድ ወረርሽኝ የተነሳ የታዛቢ ቡድኑ የሚያከናውነው የመታዘብ ተግባር የስፋት ውስንነት እንደሚኖረውና ይህንንም በሚያደርጋቸው ስራዎች እና ማጠቃለያዎች ላይ የሚገለጽ መሆኑን ታዛቢ ቡድኑ እና ቦርዱ በጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል።

ቦርዱ ከዚህ በፊት ለ45 የአገር ውስጥ የምርጫ ታዛቢዎች እውቅና መስጠቱ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post