Skip to main content

የሴት የፖለቲካ ፓርቲ አባላት የጋራ ምክር ቤት ምሥረታ ተካሄደ

ዛሬ ነሐሴ 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ሴት የፖለቲካ ፓርቲ አባላት የጋራ ምክር ቤት ምሥረታ ጉባዔ ተካሄደ። የቦርዱ አመራር አባላት የሆኑት ብዙወርቅ ከተተ፤ አበራ ደገፋ (ዶ/ር)፣ ፍቅሬ ገ/ሕይወት፣ ውብሸት አየለ እንዲሁም የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲ አባል የሆኑ ሴቶች የተሣተፉበትን ይህንን ጉባዔ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ውብሸት አየለ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ሴቶች በፓለቲካ ያላቸው ተሣትፎ እጅግ አነስተኛ እንደሆነ ገልጸው ቦርዱም ይህን እንዲሻሻል ይርዳ ዘንድ የተለያዩ ሥራዎችን ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመሥራት ቢሞክርም ከሚፈለገው ለውጥ አንጻር ግን ብዙ የሚቀሩ ሥራዎች እንዳሉ ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱን የመመሥረት ውጥን ሁለት ዓመታት እንዳሳለፈና ትልቅ ፋይዳም እንደሚኖረው ተናግረዋል።

Share this post

ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ መስከረም 20 ቀን 2014 የፓርቲ ወኪል እውቅና መታወቂያ ፍቃድ ለምትፈልጉ ፓርቲዎች በሙሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የምርጫ ስነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 እና ቦርዱን ባቋቋመው የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1133/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወኪሎች ፍቃድ ለመስጠት እና ለመከታተል የሚያስችለውን መመሪያ አርቅቆ ማጽደቁ ይታወሳል።

በዚህ መሠረት ለሚቀጥለው 10 ቀን የሚከናወነውን የመራጮች ምዝገባ ሂደትን ለመታዘብ የፓርቲ ወኪል ማቅረብ የሚፈልጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ወኪሎችን በተሰጡት ቅፆች በመጠቀም ይህ ጥሪ ከወጣበት ቀን ጀምሮ

በሶማሌ ክልል ለሚወዳደሩ- በሶማሌ ብሔራዊ ክልል የቦርዱ ጽ/ቤት

በሐረሪ ክልል ለሚወዳደሩ ፓርቲዎች- በቦርዱ ዋና መስሪያ ቤት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ለሚካሄደው ድምፅ አሰጣጥ የመራጮች ምዝገባ በሚከናወንባቸው ቦታዎች የአስፈጻሚዎች ስልጠናዎችን አከናወነ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ለሚካሄደው ድምፅ አሰጣጥ የመራጮች ምዝገባን ለማከናወን ዝግጅቶቹን እያጠናቀቀ ነው። በዚህም መሰረት ለሁለት ተከታታይ ቀናት ማለትም ነሐሴ 22 እና 23 ቀን 2013 ዓ.ም ለሐረሪ ክልል፣ ነሐሴ 23 እና 24 ቀን 2013 ዓ.ም ደግሞ ለሶማሌ ክልል እና ለደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል ለመራጮች ምዝገባ ምርጫ አስፈጻሚዎች ሥልጠናዎችን ሰጥቷል።

Share this post

መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም ለሚካሄደው ድምፅ አሰጣጥ በሶማሌ ክልል የሚከናወነው የመራጮች ምዝገባ ተጨማሪ ማብራሪያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሃሴ 17 ቀን 2013 ቀን ባሳወቀው መሰረት የመስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም የድምፅ አሰጣጥ በሚከናወንባቸው የተለያዩ ምርጫ ክልሎች የመራጮች ምዝገባ ሁኔታን አስመልከቶ ውሳኔዎች አሳለፏል። ከዚያም መካከል ተጀምሮ የነበረው የመራጮች ምዝገባ የሚቀጥልባቸው፣ የመራጮች ምዝገባ እንደአዲስ የሚከናውንባቸው እና የመራጮች ምዝገባ የማያስፈልግባቸው የምርጫ ክልሎችን ማሳወቁ ይታወሳል።

ከነዚህም መካከል የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አንዱ ሲሆን በክልሉ እየተከናወነ በነበረው የመራጮች ምዝገባ ላይ በቀረበ ከፍተኛ አቤቱታ እና ማስረጃ መሰረት ቦርዱ ማጣራት አስፈላጊ ነው ብሎ በማመኑ የአጣሪ ቡድን ተልኮ ውጤቱ እስኪወሰን ድረስ የመራጮች ምዝገባ መቋረጡ ይታወሳል። በዚህም መሰረት

1. አጣሪ ቡድን አዘጋጅቶ በ10 ምርጫ ክልሎች በማሰማራት

2. የአጣሪ ቡድኑን ሪፓርት በመገምገም

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሀገር ዐቀፍ ምርጫውን አስመልክቶ በማስተማር ላይ ከተሠማሩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ውይይት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሔሴ 17 ቀን 2013 ዓ.ም. ሀገር ዐቀፍ ምርጫውን አስመልክቶ በማስተማር ላይ ከተሠማሩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ውይይት አካሄደ። የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ፣ የቦርድ አመራር አባል የሆኑት አበራ ደገፋ (ዶ/ር) እና ብዙወርቅ ከተተ፣ እንዲሁም የቦርዱ ፅ/ቤት ሃላፊ ሜላትወርቅ ኃይሉ የተገኙበትን መድረክ የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ ባደረጉት ንግግር የተከፈተ ሲሆን፤ በንግግራቸውም ማኅበራቱ ለምርጫው ስኬታማነት የነበራቸውን ጉልህ አስተዋጽዖ ጠቅሰው አመስግነዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ምርጫ ባልተደረገባቸው ምርጫ ክልሎች ከሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት በማድረግ ቀጣዩን የድምፅ መስጫ ቀን ይፋ አድርጓል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሐሴ 13 ቀን 2013 ዓ.ም. ምርጫ ባልተደረገባቸው የምርጫ ክልሎች ከሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት አደርጓል። ሁሉም የቦርዱ አመራሮች የተገኙበትን የምክክር መድረክ በቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ አማካኝነት ቦርዱ ሲሰራቸው የቆያቸው ስራዎች ሪፓርት ለፓርቲዎች ቀርቧል። በማስከተልም ምርጫ ባልተደረገባቸው አካባቢዎች የሚኖረውን ቀጣይ የምርጫ ሂደት ከአካባቢዎቹ አጠቃላይ ሰላምና ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማገናዘብ ዝርዝር መረጃ የተሰጠ ሲሆን፤በቦርዱ ግምገማም ምርጫ ለማድረግ አመቺ ሁኔታ ያለባቸው ቦታዎችም ተለይተው ቀርበዋል። ያለውን አጠቃላይ ሁኔታ ከግንዛቤ በመክተት ቀጣዩ የድምፅ መስጫ ቀንን ጨምሮ ሌሎች ጉዳዮች ላይ ፓርቲዎች ሃሳባቸውን እንዲሰጡ ተጠይቋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባ ባልተደረገቸው እና በተቋረጠባቸው ምርጫ ክልሎችን አስመልክቶ ውሳኔ አስተላለፈ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛው አጠቃላይ ምርጫን በዋናነት ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ያስፈጸመ ሲሆን በመራጮች ምዝገባ ሂደት ላይ በታዪ ጉልህ ግድፈቶች፣ በመራጮች ምዝገባ ላይ በቀረቡ አቤቱታዎችን ለማጣራት ጊዜ በማስፈለጉ እንዲሁም ከጸጥታ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች የተነሳ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ድምፅ አሰጣጥ ያልተደረገባቸው ቦታዎች እንዳሉ ይታወቃል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስራ አመራር ቦርድ ቀሪ ምርጫ ያልተከናወነባቸው የምርጫ ክልሎችን፣ የምርጫው ሂደት ያለበትን ሁኔታ እና የመሳሰሉትን በመገምገም የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል።

የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመራጮች ምዝገባ

Share this post

በ6ተኛ አጠቃላይ ምርጫ ባልተደረገባቸው ቀሪ ቦታዎች በአስፈጻሚነት ለመሳተፍ የምትፈልጉ በሙሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛው አጠቃላይ ምርጫን ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም በዋናነት ያስፈጸመ ሲሆን በእለቱ ድምጽ አሰጣጥ ሂደት ላልተከናወነባቸው እና የመራጮች ምዝገባ በድጋሚ ለሚከናወንባቸው ቦታዎች ዝግጅቶችን ሲያደርግ ቆይቷል። ከነዚህ ስራዎችም መካከል ምርጫ አስፈጻሚዎችን ሁኔታ እና ቁጥር መገምገም አንደኛው ስራ ነው። ምርጫ አስፈጻሚዎች የምርጫ ሂደቱ ዋና አካል መሆናቸውን በመረዳት እና ስራውም ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚጠይቅ በመሆኑ እንዲሁም የምርጫ ሂደቱ ከተጀመረ በኋላ የሰው ሃይል እጥረት እንዳይፈጠር በማሰብ በሶማሌ ክልል፣ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል እንዲሁም በሐረሪ ክልል ተጨማሪ የሰው ሃይል ምልመላ ማከናወን እንዳለበት አምኗል።

በዚህም መሰረት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተካሄደውን የመራጮች ምዝገባን አስመልክቶ በባለሞያዎች አጣሪ ቡድን አማካኝነት ያካሄደውን የምርመራ ሪፓርት ለፖለቲካ ፓርቲዎች አቀረበ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም. በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተካሄደውን የመራጮች ምዝግባን አስመልክቶ በባለሞያዎች የተካሄደውን ምርመራ ለፓርቲዎች እንዲቀርብ አድርጓል። የቦርዱ ሁሉም አመራሮች የተገኙበትን የምክክር መድረክ የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ባደረጉት ንግግር የተከፈተ ሲሆን፤ የሰብሳቢዋን ንግግር ተከትሎም በምክትል ሰብሳቢው ውብሸት አየለ አወያይነት በምርምራ ላይ ከተሠማሩት ዘጠኝ ቡድኖች ተወካዮች ቀርበው በየምርጫ ክልሎቹ ያደረጉትን ምርመራ ሂደት፣ ውጤት እና ለቦርዱ የሚያቀርቡትን የውሳኔ ሃሳብ አስረድተዋል። በምርመራ ሂደቱም በቀረቡት ቅሬታዎች ላይ ቀጥተኛ ግንኙነት ካላቸው ግለሰቦች ጋር ባደረጓቸው ቃለመጠይቆች፣ በመሥክ ጉብኝት፣ ከአካባቢው ማኅበረሰብ በሰበሰቧቸው መረጃዎች፣ ከፎቶና ከተንቀሳቃሽ ምስል እንዲሁም ከቀረቡ ከተለያዩ የሠነድ ማስረጃዎችን በመጠቀም ያጠናቀሩትን ሪፖርት አቅርበዋል።

Share this post