የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ‘ለትንሳኤ ስርዓት ቓንጪ ሓቂ’ የክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሰጠ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ‘ለትንሳኤ ስርዓት ቓንጪ ሓቂ’ የክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሰጠ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ‘ለትንሳኤ ስርዓት ቓንጪ ሓቂ’ የክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሰጠ
የመድረኩ ዐላማም በምርጫ አስተዳደር አመራርነት ባሉ ሴት የቦርድ ሰብሳቢዎች መካከል የአቻ ላቻ ትብብርና ትሥሥር መፍጠር፤ እንዲሁም በአፍሪካ ደረጃ የሚያጋጥሙ ውስብስብ የምርጫ ዐውዶችን መልስ በመስጠት ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማንበር አስቻይ ሁኔታዎችን እንዴት መፍጠር ይቻላል የሚሉት ይገኙበታል። በአፍርካ ደረጃ ዘጠኝ ሴት የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢዎች ሲኖሩ፤ ኢትዮጵያ ከነዚኽ ሀገራት ውስጥ ተጠቃሽ ናት።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ወጣቶች በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ እና ሀገራዊ ኃላፊነት ጉዳዩች ዙሪያ በዕዉቀት የተደገፈ መረጃ እንዲኖራቸዉ በማስቻል ረገድ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ሴፍ ላይት ኢኒሼቲቭ ከተባለ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር የወጣቶች የማጠቃለያ የክርክር መድረክ በአዲስ አበባ ከተማ አካሒዷል፡፡
ክርክሩ በሴፍ ላይት ኢኒሼቲቭ ዋና መስሪያ ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ዉስጥ የተካሄደ ሲሆን ቀደም ሲል በጅማ እና ቢሾፍቱ ከተሞች ላይ ሲካሔድ ለቆየዉ የክርክር መድረክ ማጠቃለያ ፕሮግራም ነዉ፡፡ ክርክሩ የተካሔደዉ በዩኒቨርሲቲ እና በሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች መካከል ሲሆን ‘የፖለቲካ ፓርቲዎች ከኢኮኖሚ ፖሊሲ እና ከትምህርት ፖሊሲ የትኛዉ ላይ ትኩረት ቢያደርጉ በህዝቡ ተመራጭ ያደርጋቸዋል?’ በሚል ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ ነዉ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አንዱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እና የዜጎች ተሳትፎ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን ማዘጋጀት ዋነኛዉ ነዉ፡፡ በመሆኑም ቦርዱ ከላባ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ጋር በመተባበር፣ በአዳማ ከተማ ናፊያድ ት/ቤት በተግባር የተደገፈና ለተማሪዎች ግንዛቤን የሚያስጨብጥ የክርክር እና የምርጫ ናሙና ኹነት አካሒዷል፡፡ በመድረኩ የትምህርት ቤቱ አስተዳደር አካላትን ጨምሮ ወላጆች፣ መምህራን፣ ተማሪዎች፣ አካል ጉዳተኞች፣ ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የተዉጣጡ ጋዜጠኞች እና ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተሳትፈዋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዜጎች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርጉ እና የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ላይ የሚኖራቸዉን ተሳትፎ ለማጉላት የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ቦርዱ ከሐበጋር ዲቤትስ (ደበበ ኃ/ገብርኤል የሕግ ቢሮ) ጋር በመተባበር በሐረር ኤስ ኦ ኤስ እና በሐረር ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተማሪዎች መካከል የክርክር መድረክ አካሄዷል፡፡
የክርክሩ ፍሬ ሀሳቦች በሁለት ርዕሰ-ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ሲሆን እነርሱም፡ ለኢትዮጵያ የሚሻለዉ የፖለቲካ ሥርዓት ፕሬዝዳንታዊ ወይስ ፓርላሜንታዊ እንዲሁም የነፃ ገበያ ሥርዓት ለኢትዮጵያ ዕድገት የተሻለ ሥርዓት ነዉ ወይስ አይደለም? የሚሉ ነበሩ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትላንት ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ.ም. የሥጋት አስተዳደርና የምርጫን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ማዕቀፍን የተመለከተ ዐውደ ጥናት አካሄደ። በዐውደ ጥናቱ ላይ የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ሜላት ወርቅ ኃይሉን ጨምሮ አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት የተገኙ ሲሆን፤ የቦርዱ የየሥራ ክፍል ኃላፊዎችም ተገኝተዋል። ዐውደ ጥናቱን የቦርድ አመራር አባሏ ብዙወርቅ ከተተ በንግግር የከፈቱት ሲሆን፤ በንግግራቸውም ዐውደ ጥናቱ በዋናነት ዓላማው ያደረገው ቦርዱ ከሣምንታት በፊት ያስተዋወቀውንና ቦርዱ እንደአዲስ ከተቋቋመ ወዲህ መጀመሪያ የሆነውን የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድን በመተግበር ሂደት የተለያዩ ተግዳሮቶች ቢገጥሙት እንዴት ባለ’አግባብ ሣይንሳዊ መንገድን ተከትለን መፍታት እንችላለን፤ በዚህም ሂደት ማን ምን ሚና አለው የሚለውን መገምገምና መለየት በማስፈለጉ እንደሆነ አብራርተዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ስርዓት ዙሪያ የወጣቶች ተሳትፎን ለማጉላት ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ሰኔ 1 እና 8 ቀን 2016 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል በቢሾፍቱ እና ጅማ ከተሞች ቦርዱ ሴፍ ላይት ኢኒሼቲቭ ከተባለ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር ወጣቶች የተሳተፉበትን የክርክር መድረክ አካሔዷል፡፡ የክርክር መድረኩ መክፈቻ ፕሮግራም ሰኔ 1 ቀን 2016 ዓ.ም. በቢሾፍቱ ከተማ በርታ ደበሌ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን ቀጣይ መድረኩ ሰኔ 8 ቀን 2016 ዓ.ም. ጅማ ከተማ አሜሪካን ኮርነር የህዝብ ላይብረሪ ዉስጥ ተካሔዷል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እና የምርጫ ሂደቶች ዙሪያ ዜጎችን ለመድረስ ያስችለዉ ዘንድ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ቦርዱ ድሪም ፎር ዴቨሎፕመንት ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ከተባለ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፡ ወላይታ እና አርባ ምንጭ ከተሞች በተማሪዎች፣ አካል ጉዳተኞች እና ሴቶች መካከል ሶስት የክርክር መድረክ አካሂዷል፡፡ የክርክሩ ጭብጡም በሶስት ርዕሰ-ጉዳዮች ዙሪያ ላይ ያተኮረ ሲሆን እነርሱም፡ ለሀገር ህልዉና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ግዴታ ነዉ ወይስ አይደለም?፣ማህበረሰቡ ስለ አካል ጉዳተኞች ያለዉ የተዛባ አስተሳሰብ አካል ጉዳተኞች በምርጫ ዙሪያ እኩል ተሳትፎ እንዳይኖራቸዉ አድርጓል ወይስ አላደረገም?፣ ሴቶች በምርጫ ወቅት በመምረጥ ነው ወይስ በመመረጥ የተሻለ ተሳትፎ የሚኖራቸዉ? በሚሉ የመከራከሪያ ሀሳቦች ዙሪያ ነዉ፡፡