ስለ ጥሞና ወቅት መረጃዎች
የጥሞና ወቅት በቅድመ የምርጫ ዑደት ውስጥ የሚገኝ ጊዜ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ የምርጫ ዑደት መመሪያ መሠረት ምርጫ ከመደረጉ በፊት ያሉትን አራት ቀናት ያካትታል፡፡ በጥሞና ወቅት ታዲያ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት፤ ማለትም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ኃላፊነቶች አሉ፡፡
የፖለቲካ ፓርቲዎች
የጥሞና ወቅት በቅድመ የምርጫ ዑደት ውስጥ የሚገኝ ጊዜ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ የምርጫ ዑደት መመሪያ መሠረት ምርጫ ከመደረጉ በፊት ያሉትን አራት ቀናት ያካትታል፡፡ በጥሞና ወቅት ታዲያ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት፤ ማለትም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ኃላፊነቶች አሉ፡፡
የፖለቲካ ፓርቲዎች
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነፃ፣ ፍትሃዊ እና ተዓማኒነት ባላቸው ምርጫዎች እና የህዝብ ውሳኔዎች አማካይነት በኢትዮጵያ ዲሞክራሲን ማጎልበትንና ማፅናትን ዋና ስትራቴጂያዊ ግቡ ያደረገ ከ2016/17 ዓ.ም እስከ -2020/21 ዓ.ም የሚተገበር ስትራቴጂክ ዕቅድ ይፋ አደረገ።
ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚተገበረው የስትራቴጂክ ዕቅድ ስድስት አምዶችን (pillars) ማለትም የምርጫ ሕግ ማዕቀፍ፣ የዜጎች ተሳትፎና የግብ ትስስር፣ የምርጫ ሥራዎች፣ የምርጫ ባለድርሻ አካላት ተሳትፎና አጋርነት፣ ተቋማዊ ለውጥና ግንባታ እንዲሁም የምርጫ ቴክኖሎጂ እና ፈጠራን ማእከል አድርጎ የተዘጋጀ ነው።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕግ ከተሰጡት ኃላፊነቶች መሀከል መራጮች በቂ የምርጫ ነክ መረጃ እና ግንዛቤ የሚያገኙበትን አካታች ስልት መቀየስ እና የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም የስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርትን መስጠት አንዱ ነዉ፡፡ በዚህም መሰረት የስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርትን ለአካል ጉዳተኛ ማህበረሰቦች በቋሚነት ተደራሽ ለማድረግ በስፋት እየሠራ ይገኛል፡፡ይህንን ተከትሎ ግንቦት 27 ቀን 2016 ዓ.ም የተለያዩ በብሬል የተዘጋጁ የህትመት ዉጤቶችን፣ ማለትም ምርጫ በኢትዮጵያ በሚል ርዕስ የተዘጋጂ ቡክሌቶች፣ እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና ስነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 አዋጆችን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኬኔዲ እና ሕግ ላይብረሪ ክፍል አስረክቧል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ የአፋር፣ የሶማሌ እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው ቤንሻንጉል ጉሙዝ ፣አፋር ሶማሌ እና መስቃን እና ማረቆ-2 የምርጫ ክልሎች ላይ የእጩዎች ምዝገባ ከሚያዝያ 21 አስከ ግንቦት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. ማከናወኑ ይታወቃል። በመሆኑም የምርጫ ሕጉ ተወዳዳሪ እጩዎችን ቦርዱ ለህዝብ ይፋ እንዲያደርግ በደነገገው መሰረት ቦርዱ በቦርዱ የተረጋገጡ የእጩዎችን ዝርዝር ከዚህ በታች ይፋ አድርጓል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ የአፋር፣ የሶማሌ እና የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ለሚያካሂደው ምርጫ የተለያዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ከነዚህም ተግባራት አንዱ የዕጩዎች ምዝገባ ሲሆን፤ በትላንትናው ዕለት ማለትም ግንቦት 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የተመዘገቡ ዕጩዎችን በድምፅ መስጫ ወረቀቱ ላይ የሚኖራቸውን የአደራደር ቅደም ተከተል የሚወሥነውን የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት አካሂዷል።
በዚህ የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት ላይ የቦርዱ ዋና ሰብሳቢን ጨምሮ ሁሉም የቦርድ አመራር አባላትና በምርጫው ላይ የሚሣተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዩች የተገኙ ሲሆን፤ ሥነ-ሥርዓቱም የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ተከፍቷል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ የአፋር፣ የሶማሌ እና የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ለሚያካሂደው ምርጫ የተለያዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ይህንንም ተከትሎ የመራጮች ምዝገባ ከሚያዚያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ በመከናወን ላይ በሚገኝባቸው በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በአፋር እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች የቦርዱ የበላይ ኃላፊዎች የመሥክ ጉብኝት እና ውይይት ከግንቦት 7-8 ቀን 2016 ዓ.ም. አካሂደዋል፡፡
በመስክ ጉብኝቱ በምርጫ ክልሎቹ ላይ እየተከናወነ ያለውን የምርጫ ነክ ሥራዎች ምን እንደሚመስሉ ከመመልከታቸው በተጨማሪ፤ በምርጫ ጣቢያዎቹ በመከናወን ላይ ያለውን የመራጮች ምዝገባ አጠቃላይ ሁነትን የተመለከቱ ሲሆን በየምርጫ ጣቢያዎቹ በሥራ ላይ ከነበሩ ከመራጮች ምዝገባ አስፈጻሚዎች ጋር ውይይት ተደርጓል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛውን ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. እንደሚያከናውን ይታወቃል ነገር ግን ስማችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘረው ግለሰቦች በ 2013 ዓ.ም በ6ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ወቅት እጩ የነበራችሁ ሲሆን አሁን በምናደርገው ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ እንድትሳተፉ በቦርዱ የመረጃ ቋት ውስጥ ባላችሁ ስልክ ቁጥር በመደወል ለማግኘት የተደረገው ጥረት ስልካችሁ ሊሰራ ባለመቻሉ ምክንያት ሊሳካ አልቻለም። ይሁን እንጂ ቦርዱ በምርጫ አዋጁ 1162/2011 አንቀጽ 39 (2) መሰረት የእጩዎችን የመወዳደር መብት ለመጠበቅ የመጨረሻ ማጣራት እያከናወነ ይገኛል፡፡
በዚህ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘረው ግለሰቦች አስከ ግንቦት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. እስከ ጠዋቱ አራት ሰዓት ድረስ በስልክ ቁጥር 0995003794 በመደወል እንድታሳውቁ ቦርዱ ጥሪ ያቀርባል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛውን ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. እንደሚያከናውን ይታወቃል፡፡ ለዚህም ይረዳ ዘንድ የዕጩ ምዝገባ ከሚያዝያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን ስማችሁ ከዚህ በታች የተገለጹት የፓርቲያችሁ አባላት በዚህ ምርጫ እንደማይሳተፉ እና በሌላ እጩ መተካታቸውን አሳውቃችሁናል፡፡ ይሁን እንጂ ቦርዱ በምርጫ አዋጁ 1162/2011 አንቀጽ 39 (2) መሰረት የእጩዎችን የመወዳደር መብት ለመጠበቅ የመጨረሻ ማጣራት እያከናወነ ይገኛል፡፡
በመሆኑም ግለሰቦችን በቦርዱ የመረጃ ቋት ውስጥ ባላቸው ስልክ ቁጥር በመደወል ለማግኘት የተደረገው ጥረት ስልካቸው ሊሰራ ባለመቻሉ ምክንያት ሊሳካ አልቻለም። በዚህ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘረው ግለሰቦች ከፖለቲካ ፓርቲያችሁ መልቀቃቸሁን ለፓርቲያችሁ እንድታሳውቁ እና መልቀቃችሁን የሚገልጽ ሰነድ ለቦርዱ እንድትልኩ እንጠይቃለን።
የመገናኛ ብዙኃን ቀጣዩ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ምርጫው ፍትሐዊ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ እንዲሆን የሚያበረክቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ፤ የመገናኛ ብዙኃኑና ጋዜጠኞች በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው ለመዘገብ የሚያስችል የፍቃድ ጥያቄያቸውን ለቦርዱ እንዲያቀርቡ ይህንን ጥሪ ማድረግ አስፈልጓል፡፡ በዚህ መሠረት ለመዘገብ ጥያቄ የሚያቀርቡ የመገናኛ ብዙኃን፡