የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. የሚያደርገውን የ6 ኛው ዙር ቀሪና የድጋሚ ምርጫን ለመዘገብ ከቦርዱ እውቅና ላገኙ የመገናኛ ብዙኃን ሰኔ 12 ቀን 2016 ዓ.ም. ሥልጠና ሠጠ፡፡
ስልጠናው የመገናኛ ብዙኃን እና የጋዜጠኞች የምርጫ አዘጋገብ ስነ ምግባርን ላይ አትኩሮት አድርጎ የምርጫ ዑደትና የምርጫ ሕግ ማዕቀፍን፤ ምርጫውን የተመለከቱ አጠቃላይ መረጃዎችን፤ አካታች የምርጫ ዘገባ ባህሪያትን እና የተዛቡ፤አሳሳች፤አደናጋሪና በአጋጣሚ ወይም ሆን ተብለው የሚፈጠሩ የመረጃ መዛባቶችን እና የመረጃዎችን ትክክለኛነት ለመፈተሽ በሚያስችሉ የዲጂታል እውቀቶች እና አጠቃቀሞች ዙሪያ ያተኮረ ነበር፡፡