Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሁሉም ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች የፃፈዉ ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዚህ ደብዳቤ በተገለጸው መሰረት ለሁሉም ደብዳቤ ለደረሳቸው ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች እስከ ነገ ሰኔ 13 ቀን 2013 ዓ.ም እኩለ ቀን ድረስ ይህንን ማዘጋጀታቸውን በጽሁፍ እንዲያረጋግጡ እና በደብዳቤ፣ በኢሜይል፣ ወይም በማንኛውም ኤሌክትሮኒክ መንገድ እንዲያሳውቁ ለማሳሰብ ይወዳል።

ለአዲስ አበባ ከተማ

ለአፋር ክልል

አንድ መራጭ ለክልል ምክር ቤት መቀመጫ ምን ያህል እጩዎችን መምረጥ ይችላል?

ለክልል ወይም ለከተማ ም/ቤት መቀመጫ አንድ መራጭ መምረጥ የሚችለው የእጩዎች ብዛት እንደየምርጫ ክልሉ ይለያያል ። አንዳንድ የምርጫ ክልሎች ላይ 1 እጩ፣ እንዳንድ የምርጫ ክልሎች ላይ 3 እጩዎች አንዳንድ የምርጫ ክልሎች ደግሞ ላይ 9 እጩዎች አንዳንድ የምርጫ ክልሎች ላይ 14 እጩዎች ወይም ሌላ ቁጥር ያለው የመቀመጫ ብዛት ሊኖራቸው ይችላል።

ብዛቱ የሚወሰነው የምርጫ ክልሉ በክልል ም/ቤቱ ባለው የመቀመጫ ቁጥር ብዛት ነው ። በመሆኑም አንድ መራጭ በክልል ም/ቤት ድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ መምረጥ የሚችለው የዕጩዎች ብዛት በክልል ምክር ቤት ድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ ከላይ ተፅፎ ይገኛል። በዚህም መሰረት አስፈጻሚዎች የድምፅ መስጫ ወረቀት ሲሰጡ ለመራጩ በምርጫ ጣቢያ ውስጥ እስከ ስንት እጩ መምረጥ እንደሚችል ያስረዳሉ።

ለምርጫ ክልል ምርጫ አስፈጻሚዎች በሙሉ

ሰኞ ሰኔ 14 ቀን ለሚከናውነው አጠቃላይ ምርጫ የፓርቲ ወኪሎችን እውቅና ባጅ የመስጠት ስራ እያከናወናችሁ እንደሆነ ይታወቃል። ካለው አጭር ጊዜ አንጻር የእጩ ወኪሎች ባጅ መስጠትን እስከ ነገ ማታ ሰኔ 13 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ እንድታከናውኑ እናሳስባለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኦፕሬሽንስ የስራ ክፍል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 11 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 11 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:30 በስካይ ላይት ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

  • በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣
  • የቦርዱን ልዩ የዘገባ ባጅ ፊት ለፊት ማንጠልጠል
  • ከአንድ ሚዲያ ሁለት ባለሞያዎች (የፎቶ/የቪዲዮ ባለሙያን ጨምሮ) ብቻ መሣተፍ ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 10 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 10 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:30 በስካይ ላይት ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

•በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣

•የቦርዱን ልዩ የዘገባ ባጅ ፊት ለፊት ማንጠልጠል

•ከአንድ ሚዲያ ሁለት ባለሞያዎች (የፎቶ/የቪዲዮ ባለሙያን ጨምሮ) ብቻ መሣተፍ ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

መረጃ ለግል እጩ ተወዳዳሪዎች

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከግል እጩ ተወዳዳሪዎች ጋር በተለያየ ግዜ ባደረገው ምክክር መሰረት ቦርዱ የግል እጩ ተወዳዳሪዎች የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው አምኖበት ለእያንዳንዳቸው የ50 ሺህ ብር ድጋፍ ለመስጠት ወስኗል፡፡

ስለሆነም በምርጫ ቦርድ በግል እጩ ተወዳዳሪነት እውቅና አግኝታችሁ ለ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ የምትወዳደሩ ሁሉ ሙሉ ስማችሁን አድራሻችሁን (ስልክ ቁጥራችሁን፣ ኢሜል) እንዲሁም የባንክ አካውንታችሁን ለፖለቲካ ፓርቲዎች ስራ ክፍል በአካል ወይም በ politicalparties@nebe.org.et ኢሜል አድራሻ ወይም በስልክ ቁጥሮች +251913551505/ +251929289444 የዋትስ አፕ እና ቴሌግራም አፕሊኬሽኖች ላይ እንድትልኩ እናሳውቃለን፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሰኔ 09 ቀን 2013 ዓ.ም

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 09 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 09 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:30 በስካይ ላይት ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

  • በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣
  • የቦርዱን ልዩ የዘገባ ባጅ ፊት ለፊት ማንጠልጠል
  • ከአንድ ሚዲያ ሁለት ባለሞያዎች (የፎቶ/የቪዲዮ ባለሙያን ጨምሮ) ብቻ መሣተፍ ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሰኔ 09 ቀን 2013 ዓ.ም

ስለ ጥሞና ወቅት መረጃዎች

የጥሞና ወቅት በቅድመ የምርጫ ዑደት ውስጥ የሚገኝ ጊዜ ሲሆን በኢትዮጵያ የምርጫ ዑደት መመሪያ መሠረት ምርጫ ከመደረጉ በፊት ያሉትን አራት ቀናት ያካትታል፡፡ በጥሞና ወቅት ታዲያ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት፤ ማለትም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመገናኛ ብዙሀን ተቋማት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ሀላፊነቶች አሉ፡፡

የፖለቲካ ፓርቲዎች

Share this post