የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ኮንግረስ ፓርቲ ከሀገር ዓቀፍ የፖለቲካ ፓርቲነት እንዲሰረዝ የኢትጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የወሰነውን ውሳኔ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመቀበል የሰጠው ውሳኔ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ኮንግረስ በአዋጅ ቁጥር 1162/11 መሰረት በሀገር ዓቀፍ ፓርቲነት ለመመዝገብ ጥያቄ አቅርቦ በአዋጁ አንቀጽ 64 መሰረት ፓርቲው ከአምስት ክልሎች ማቅረብ የሚገባውን አስር ሺህ (10,000) የመስራች አባላት በቁጥር ያቀረበ ቢሆንም የክልላዊ አባላት ስብጥርን በሚመለከት ግን ከአንድ ክልል መሟላት ከሚገባው አንድ ሺህ አምስት መቶ (1,500) መስራች አባላት ውስጥ አንድ ሺህ አርባ አምስት (1,045) መስራች አባላት ብቻ ያቀረበ በመሆኑ ለሀገር ዓቀፍ የፖለቲካ ፓርቲ የሚያስፈልገውን የመስራች አባላት ክልላዊ ስብጥር አሟልቶ ስላልቀረበ ከየካቲት 29 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ከፖለቲካ ፓርቲነት እንዲሰረዝ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ወስኖ ነበር፡፡