Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው አጠቃላይ ምርጫ ድምፅ መስጠት ሂደት ጋር ተያይዞ አቤቱታ ካቀረቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 22 ቀን 2013 ዓ.ም. በ6ኛው አጠቃላይ ምርጫ ተሣትፈው በድምፅ መስጠት ሂደቱ ላይ አቤቱታ ካቀረቡ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር አድርጓል። የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳና የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ውብሸት አየለ በተገኙበት የተከናወነው የምክክር መድረክ፤ በፓርቲዎች የቀረቡ አቤቱታዎችን መፍትሔ ለመስጠት ቦርዱ በሚከተለው ሥርዓት ላይ ካለው ጊዜ አንጻር ፓርቲዎቹ ፈጣንና የተሻለ መፍትሔ ለማግኘት ይረዳል ያሏቸውን የማዳበሪያ ሃሳቦች እንዲያጋሩ ለማስቻል ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ ሲሆን፤ ይህንንም የቦርዱ ሰብሳቢና ምክትል ሰብሳቢ በንግግራቸው ገልጸውታል። የቦርዱ የህግ ክፍል ሃላፊም በምክክሩ የተገኙ ሲሆን አቤቱታዎች ሊኖራቸው የሚገባውን ቴክኒካል ይዘት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

Share this post

ማስታወቂያ በ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ የተሳተፋችሁ የፓለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ

6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ሂደት ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም መከናወኑ ይታወሳል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በእለቱ የፓለቲካ ፓርቲዎች አቤቱታ ዴስክ በማቋቋም በስልክ፣ በአጭር መልእክት፣ በደብዳቤ አቤቱታዎችን ሲቀበል እና በእለቱ መፈታት የሚችሉትን ችግሮችም ሲፈታ መቆየቱ ይታወሳል።>/p>

ቦርዱ ከድምፅ መስጫው ቀን በማስከተል በተለያየ ሁኔታ የቀረቡትን አቤቱታዎች ሲመለከት እና ሲመረምር ቆይቷል። አንዳንዶቹ አቤቱታዎች በየደረጃው በሚከናወነው የምርጫ ሂደት መቅረብ የነበረባቸው እና በምርጫ ክልሎች እና ጣቢያዎች ደረጃ የሚቀርቡ ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ ቦርዱ በምርመራ የሚያያቸው ናቸው። ቦርዱ ከአቤቱታዎቹ የተቆራረጡ፣ ሙሉ መረጃ ያልያዙ እና መካተት የሚገባውን መረጃዎች ያካተቱ ባለመሆናቸው ምርመራውን አስቸጋሪ መሆኑን ተረድቷል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኔ 17 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ የሚዲያ ማብራሪያ ይሰጣል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኔ 17 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ የሚዲያ ማብራሪያ ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:30 ስካይላይት ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

•በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣

•የቦርዱን ልዩ የዘገባ ባጅ ፊት ለፊት ማንጠልጠል

•ከአንድ ሚዲያ ሁለት ባለሞያዎች (የፎቶ/የቪዲዮ ባለሙያን ጨምሮ) ብቻ መሣተፍ ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለክልል እና ለከተማ አሰተዳደሮች የምርጫ ክልል ሃላፊዎች የውጤት ሰነዶቻቸውን ወደማእከል በሚያመጡበት ወቅት ሊሰጣቸው የሚገባውን ትብብር አስመልክቶ ያቀረበው ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ክልል ደረጃ የውጤት ድመራ ተጠናቆ ምርጫ ክልል ሃላፊዎች ወደ ማእከል ሰነዶችን ይዘው እንዲመጡ እንደሚያደርግ ይታወቃል። በመሆኑም የክልል መስተዳድሮች የምርጫ ክልል ሃላፊዎች እና የውጤት ሰነዶቻቸውን ወደማእከል በሚያመጡበት ወቅት ሊሰጣቸው የሚገባውን ትብብር አስመልክቶ ቦርዱ ያቀረበው ደብዳቤ

ደብዳቤዉን ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

መራጭ ዜጎች፣ ለምርጫ አስፈፃሚዎች ፣ ለሚመለከታቸው አካላት በሙሉ

እንደሚታወቀው የ6ተኛው አገራዊ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ እየተከናወነ ይገኛል።

1, የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ዘግይቶ የተጀመረባቸው ቦታዎች በመኖራቸው

2, የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ላይ የቁሳቁስ ስርጭት የዘገየባቸው ቦታዎች በመኖራቸው

3, ድምፅ ለመስጠት ረጅም ሰልፉች ላይ ያሉ ዜጎች በመኖራቸው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት እስከ ምሽቱ 3 ሰአት ድረስ መራዘሙን ቦርዱ ያሳውቃል። በዚህም መሰረት የምርጫ አስፈፃሚዎች እስከ 3 ሰአት ድረስ የሚመጣ ማንኛውንም መራጭ እንዲያስተናግዱ ጥሪ እናስተላልፋለን። ነገር ግን የመራጮች መዝገባቸው ላይ ያሉ ዜጎች መርጠው ያጠናቀቁባቸው እና ለመምረጥ የተሰለፉ ዜጎች በተጠናቀቁበት ቦታዎች የምርጫ ጣቢያ መዝጋት እና የቆጠራ ስራ መጀመር ይችላሉ።

በድምፅ አሰጣት ሂደት ወቅት ችግር ያጋጠማቸው ዜጎች 778 ነጻ የስልክ መስመር በመደወል ማሳወቅ ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የምርጫ ቀን በምስል

ዜጎች በአብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ድምጽ እየሰጡ ሲሆን ከምርጫ ጣቢያዎች የተወሰኑት ይህንን ይመስላሉ

Share this post

ስለ ድምፅ መስጫ ቀን በጥቂቱ

በድምጽ መስጫ ቀን የተከለከሉ ተግባራት ምን ምን ናቸው?

  • ማንኛውም ሰው ከምርጫ ጣቢያው 200 ሜትር ዙሪያ መለስ ርቀት ውስጥ በስካር መንፈስ ውስጥ ሆኖ፣ የጦር መሣሪያ ይዞ ወይም በሌላ በማናቸውም ፀጥታን በሚያደፈርስ ሁኔታ ውስጥ መገኘት የለበትም
  • መራጭ ያልሆኑና ድምፅ የሰጡ ሰዎች በምርጫ ጣቢያው ውስጥ መገኘት የለባቸውም
  • ማንኛውም ሰው ያለፈቃድ ወደምርጫ ጣቢያው በመግባት ወይም በምርጫ ጣቢያው ግቢ ውስጥም ሆነ ውጭ የምርጫውን እንቅስቃሴ ማወክ ወይም ማደናቀፍ ወይም
  • ምንም አይነት የምርጫ ቅስቀሳ እንቅስቃሴ ማድረግ የለበትም

ወደ ምርጫ ጣቢያ የማይገቡ ነገሮች ምንድናቸው?

ድምፅ ለመስጠት ብቁ የሆኑ እነማን ናቸው?

1. ድምፅ ለመስጠት በተመዘገበችበት የምርጫ ጣቢያ የተገኘች መራጭ፡-

ሀ) የመራጮች ምዝገባ መታወቂያ ካርድ ያላት፣

ለ) የማንነት ማረጋገጫ መታወቂያ ወይም በመራጮች ምዝገባ ወቅት የተረጋገጠበት ሌላ ሰነድ ያላት፣ወይም ማንነትዋ በምርጫ ምዝገባ ወቅት በምስክሮች ስለመረጋገጡ

በመራጮች መዝገብ ላይ የሰፈረላት፣

ሐ) የመራጮች መዝገብ ላይ ስሟ የሰፈረ፣

መ) ድምፅ ያልሰጠች መሆኑ ሲረጋገጥ ድምጿን የመስጠት መብት አላት

2. የመራጮች ምዝገባ መታወቂያ የጠፋባት መራጭ ጉዳዩን ለምርጫ ጣቢያው በማስረዳት ማንነቷ እንዲሁም በመዝገቡ ላይ ስሟ የሰፈረና ያልመረጠች መሆኑ ሲረጋገጥ ጉዳዩ በቃለ ጉባኤ ተይዞ እንድትመርጥ ይደረጋል፡፡

ድጋፍ ስለሚፈልጉና ቅድሚያ ስለሚሰጣቸው መራጮች

1. የምርጫ ጣቢያው ሀላፊ አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞችን፣ ነፍሰጡሮችን፣ ጨቅላ ህጻናት የያዙ ወላጆችን፣ መለዮ የለበሱ የመከላከያና የፖሊስ አባላትን ቅድሚያ በመስጠት ድምፅ እንዲሰጡ ማድረግ አለበት

2. በድምፅ አሰጣጡ ሂደት ምልክት ለማድረግና የድምፅ መስጫ ወረቀቱን ወደሳጥን ለመክተት እገዛ የሚያስፈልገው መራጭ ራሱ የመረጠውን ሰው ይዞ የመምጣት መብት አለው

3. በዚህም መሰረት በድጋፍ ፈላጊው የሚመረጥ ሰው :-

ሀ) ዕድሜው 18 ዓመትና ከዚያ በላይ መሆን አለበት

ለ) እጩ ተወዳዳሪ ወይም የእጩ ወኪል መሆን የለበትም

4. አንድ ድጋፍ የሚሰጥ ሰው ከአንድ በላይ መራጭ ለመደገፍ አይችልም

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሁሉም ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች የፃፈዉ ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዚህ ደብዳቤ በተገለጸው መሰረት ለሁሉም ደብዳቤ ለደረሳቸው ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች እስከ ነገ ሰኔ 13 ቀን 2013 ዓ.ም እኩለ ቀን ድረስ ይህንን ማዘጋጀታቸውን በጽሁፍ እንዲያረጋግጡ እና በደብዳቤ፣ በኢሜይል፣ ወይም በማንኛውም ኤሌክትሮኒክ መንገድ እንዲያሳውቁ ለማሳሰብ ይወዳል።

ለአዲስ አበባ ከተማ

ለአፋር ክልል