የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባኤ አስመልክቶ የሰጠው ውሳኔ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባኤ አስመልክቶ የሰጠው ውሳኔ ሙሉ መግለጫዉን ለማግኘት እዚህ ላይ የጫኑ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባኤ አስመልክቶ የሰጠው ውሳኔ ሙሉ መግለጫዉን ለማግኘት እዚህ ላይ የጫኑ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ጠቅላላ ጉባኤ ማካሄዱን ተከትሎ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን ለቦርዱ ሪፓርት አቅርቧል፡፡ ቦርዱም ፓርቲው ያወጣውን ማሻሻያ ደንብ በመመርመር ያልተሟሉ ጉዳዮች ላይ ማስተካከያ እንዲያደርግ ውሳኔውን ያሳወቀበት ደብዳቤ ከስር ያገኙታል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነፃነት ንቅናቄ ፓርቲ (ኦነን) ጠቅላላ ጉባኤውን አስመልክቶ የቀረቡ አጠራጣሪ ሰነዶችን አስመልክቶ ምርመራ እንዲደረግ ለፌደራል ፓሊስ ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን ምርመራው ተጣርቶ እስኪጠናቀቅ ፓርቲው በአዋጅ 1162/2011 አንቀፅ 98/3 መሰረት መታገዱን ይገልፃል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ባካሄደው ምክክር ወቅት ይፋ ያደረገው ለፓርቲዎች የሚሰጥ የገንዘብ ድጋፍ መጠን ከስር ይገኛል። የገንዘብ ድጋፉ ከዚህ ቀደም በፀደቀው መመሪያ ላይ በተቀመጡ መስፈርቶች መሰረት የተከናወነ ነው።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኦነግ አመራሮች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት አስመልክቶ የቀረቡለትን አቤቱታዎች በማየት ውሳኔ መስጠቱ ይታወሳል። በውሳኔው ቅር የተሰኙት የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር እነ አራርሶ ቢቂላ ጉዳዮን ወደፍርድ ቤት በመውሰዳቸው ክርክር ሲደረግበት ቆይቶ የሰበር ሰሚ ችሎት የሁለቱንም ወገኖች የመሰማት መብት በመጠበቅ አስተዳደራዊ ውሳኔ እንዲሰጥበት ወደቦርዱ መልሶታል። በዚህም መሰረት ቦርዱ የተለያዩ ምርመራዎችን በማድረግ የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ ተከትሎ ያሳለፈው ውሳኔ የሚከተለው ሲሆን ለሁለቱም ተከራካሪ ቡድኖች እንዲደርስ ተደርጓል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአዲስ አበባ ዋና መስሪያ ቤት እና ለክልል ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶች በተለያዩ የስራ መደቦች ተፈላጊውን የስራ ችሎታ እና ልምድ የሚያሟሉ ስራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡ ፍላጎት ያላችሁ እና መስፈርቱን የምታሟሉ ሁሉ ከታች የሚገኘውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም እንድታመለክቱ እናበረታታለን፡፡
አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣ በ10 ቀናት ውስጥ በኢሜል አድራሻችን hr.dept [at] nebe.org.et ብቻ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 26 የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርጉ ባስታወቀው መሰረት የፓርቲዎች የጠቅላላ ጉባኤ ሲያካሂዱና ለማካሄድም ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል። በዚህም መሰረት የፓርቲዎች የጠቅላላ ጉባኤ ሁኔታ ማጠቃለያ የሚከተለውን ይመስላል።
ጠቅላላ ጉባኤ ያካሄዱ ፓርቲዎች
ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ በጊዜ ገደቡ መሰረት ቀን ያሳወቁ ፓርቲዎች
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህዳር 23 ቀን 2014 ከፓርቲዎች ጋር ባደረገው ምክክር በአዋጅ ቁጥር 1162/11 እና በመመሪያ ቁጥር 3/2011 መሠረት ከ6ተኛው አገራዊ ምርጫ መጠናቀቅ በኋላ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያካሂዱና የሰነድ ማሻሻያ እንዲያደርጉ የተገለፀላቸው ፓርቲዎች የሚጠበቅባቸውን አጠናቀው ባለማቅረባቸው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በተነሳ በአንድ ወር ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤያቸውን እንዲያከናውኑ እና ለቦርዱ እንዲያስገቡ መወሰኑ በምክክሩ ወቅትም ለፓርቲዎች መገለጹ ይታወሳል።
በዚህም መሰረት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በትላንትናው እለት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ መወሰኑን ተከትሎ ከስር ስማችሁ የተዘረዘረ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ በማከናወን እንዲሁም አስፈላጊ የሰነድ ማሻሻያዎችን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በማድረግ እንድታስገቡ እናሳስባለን።
አገራዊ ፓርቲዎች