የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚደረግባቸው አካባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያየ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት መጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም. 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚደረግባቸው አካባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያየ። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉን ጨምሮ አምስቱም የቦርድ ሥራ አመራር አባላት በተገኙበት በተደረገው ውይይት ላይ ቦርዱ ቀደም ሲል ከፖለቲካ ፓርቲዎች የሰበሰበው ሥጋት አለባቸው ብለው የለዩዋቸው አካባቢዎች ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፤ በውይይቱ ከተነሡ ተጨማሪ አጀንዳዎች ውስጥም በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ ያለ የፀጥታ ሥጋትና በነፃነት የምረጡኝ ቅስቀሳ ያማድረግ ሁኔታ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ያለምንም ተፅዕኖ ሥራቸውን ማከናወን፣ የፖለቲካ ምኅዳርን በተመለከተ የተቸገሩ መሆኑ ይጠቀሳሉ።