የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለባሕር ዳር እና ለአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በጎ-ፈቃደኛ ተማሪዎች በሥነ-ዜጋና በመራጮች ትምህርት ላይ ያተኮረ ሥልጠና ሰጠ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዜጎች የሥነ¬-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ላይ የተሻለ መረዳት እንዲኖራቸው ለማስቻል በማሰብ በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ለሚገኙ በጎ-ፈቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠና መስጠት መጀመሩ ይታወቃል። ቀደም ሲል ቦርዱ ለአዲስ አበባ፣ ለሰመራ እንዲሁም ለድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በጎ-ፈቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠናውን የሰጠ ሲሆን፤ አሁን ደግሞ ለባሕር ዳር እና ለአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በጎ-ፈቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠናውን ሰጥቷል።