በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርት የስራ ክፍል ከቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት በክልሉ ከሚገኙ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር የወጣቶች የበጎ ፈቃድ ስልጠናን አስመልክቶ ምክክር አደረገ።
የቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት የሥራ ክፍል ባለሙያ በጋራ በመሆን በስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት ዙሪያ ከቦርዱ ጋር እየሰሩ ለሚገኙ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንዲሁም ከሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለተውጣጡ የተማሪ ተወካዮች ትምህርቱን በክልሉ ለሚገኙ ልዩ ልዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች በስፋት ማዳረስ ስለሚቻልበት ዘዴ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶቹ በበኩላቸው በሚቀጥለው ዓመት የሚደረገውን 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ታሳቢ ያደረገ እቅድ ነድፈው የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርትን በተጠናከረ መልኩ ለመስጠት ዝግጅት እንደሚያደርጉ የገለጹ ሲሆን የተማሪዎች ተወካዮች በበኩላቸው ትምህርቱን በየትምህርት ቤታቸው በሚገኙ ሚኒ ሚድያዎችና በየወቅቱ በሚደረጉ ሁነቶች ለተማሪዎች ለማሰራጨት ማቀዳቸውን ገልጸው ቦርዱ ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል። የቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የስነ ዜጋና መራጮች ትምህርት የስራ ክፍል ባለሙያ ትምህርቱን በዘላቂ