Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለባሕር ዳር እና ለአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በጎ-ፈቃደኛ ተማሪዎች በሥነ-ዜጋና በመራጮች ትምህርት ላይ ያተኮረ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዜጎች የሥነ¬-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ላይ የተሻለ መረዳት እንዲኖራቸው ለማስቻል በማሰብ በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ለሚገኙ በጎ-ፈቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠና መስጠት መጀመሩ ይታወቃል። ቀደም ሲል ቦርዱ ለአዲስ አበባ፣ ለሰመራ እንዲሁም ለድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በጎ-ፈቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠናውን የሰጠ ሲሆን፤ አሁን ደግሞ ለባሕር ዳር እና ለአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በጎ-ፈቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠናውን ሰጥቷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሴት እና አካል ጉዳተኛ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ፖለቲካዊ ተሣትፏቸና የሚደርሱባቸው ተግዳሮቶችን የተመለከተ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሴት እና አካል ጉዳተኛ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ፖለቲካዊ ተሣትፏቸውና የሚደርሱባቸው ተግዳሮቶችን የተመለከተ ሥልጠና ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 4 ቀን 2017 ዓ.ም.

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቴክኖሎጂ የታገዘ የምርጫ አስተዳደር ሥርዓት መተግበሪያውን ለባለድርሻ አካላት አስተዋወቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቴክኖሎጂ የታገዘ የምርጫ አስተዳደር ሥርዓት መተግበሪያውን ለፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ተወካዮች እንዲሁም ለሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች አስተዋወቀ። ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም. የተካሄደውን የማስተዋወቂያ መርኅ-ግብር በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ቦርዱ የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን ማስፈጸሙ ተከትሎ የምርጫ ሥርዓቱን ለማዘመን ያግዛሉ ያላቸውን በርካታ ሥራዎች ሲሠራ መቆየቱን አስታውሰው፤ ከነዚኽም ውስጥ በባለድርሻ አካላት በተለያዩ ጊዜ አስተያየት ሲሰጥበት የነበረው ዘመናዊ የምርጫ አስተዳደር ሥርዓትን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመሥራት መራጮችና ዕጩዎች በቴክኖሎጂ ታግዘው የሚመዘገቡበትን መተግበሪያ ማበልጸጉን ተናግረዋል።

Share this post

ቦርዱ “የማኅበረሰብ ቲያትር ለአካታች የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት" የተሰኘው መርኅ-ግብር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ “የማኅበረሰብ ቲያትር ለአካታች የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት” የተሰኘ መርኅ ግብር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን አካሄደ። በተጠናቀቀው ግንቦት ወር 2017 ዓ.ም. ለተከታታይ ዘጠኝ ቀናት የተካሄደው መርሐ-ግብር ማስጀመሪያ በወላይታ ሶዶ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ መሰናዶ ትምህርት ቤት የተካሄደ ሲሆን፤ በትምህርት ቤት ውስጥ ያሉትን ከ74 በላይ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ከግምት ውስጥ በማስገባትም በሥነ-ሥርዓቱ ላይ አካታችነትን የሚያስተምረውን ቲያትር መስማት ለተሳናቸው ታዳሚያን በቀጥታ ተተርጉሞ ቀርቧል።

Share this post

ቦርዱ የ6ኛው ሀገራዊ ምርጫን ተከትሎ በወሰዳቸው ሦስት ቁልፍ የምርጫ ሥርዓት ማዘመኛ ማሻሻያዎችን በተመለከተ ዎርክሾፕ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን መፈጸም ተከትሎ ሁሉምን ባለድርሻ አካላት፤ መገናኛ ብዙኃኑን ጨምሮ በተናጠል የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን ስኬትና ተግዳሮት ተብለው ሊጠቀሱ የሚችሉትን ጉዳዮች በዝርዝርና በጥልቀት በመወያየት፤ የውይይቱንም ግኝት (Lesson Learned) ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በአንድ ላይ ባሣተፈ መልኩ በድጋሚ አስተችቶ የማሻሻያ መፍትሔዎችን መውሰድን የቅድሚያ ቅድሚያ ተግባሩ አድርጎ ሲሠራ ቆይቷል።

ቦርዱ በባለድርሻ አካላት ማሻሻያ ተጠይቆባቸው የመፍትሔ ዕርምጃ ከወሰደባቸው ዋና ዋና አጀንዳዎች ውስጥ ለአፈጻጸም አስቸጋሪ የነበሩትን የዐዋጁ አንቀጾችን በመለየት ሀገራዊ ተጨባጭ ሁኔታዎችን እና ዓለም ዐቀፍ ተሞክሮዎችን ባገናዘበ መልኩ የማሻሻያ ሃሳቦችን በባለሞያ አስጠንቶ ማቅረብ፣ የዕጩዎችንና የመራጮችን መጉላላት የሚያስቀር እና መረጃንም ዘመናዊ ሥርዓትን ጠብቆ ለማደራጀት የሚያግዝ የዲጂታይዜሽን ሥራ መሥራት ይጠቀሳሉ።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ርዕሰ-ጉዳይ ላይ የሰጠው የአሠልጣኞች ሥልጠናን የተመለከተ የልምድ ልውውጥ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሀገሪቱ ውስጥ ባሉ የተለያዩ ብሔራዊ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ላሉ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ርዕሰ-ጉዳይ ላይ ሥልጠና በመስጠት ላይ መሆኑ ይታወቃል። ይኽንንም ተከትሎ ቦርዱ ቀደም ሲል ሥልጠናውን በተሰጠባቸው በሲዳማ እና በአፋር ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ እና በድሬደዋ ከተማ መስተዳድሮች “በሙከራ ትግበራ ማዕቀፍ” ከአራት ዩኒቨርሲቲዎች ለተውጣጡ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በሥነ-ዜጋና በመራጮች ትምህርት ርዕሰ-ጉዳይ ላይ የሰጠው የአሠልጣኞች ሥልጠና ያስገኘው ውጤትና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች፤ እንዲሁም የትኞቹ የሥልጠና ሥልቶች ውጤት አስገኙ የሚለው ላይ የልምድ ልውውጥ አካሄደ።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰመራ ዩኒቨርሲቲ እና ለድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በድኅረ ምርጫ ወቅት ከሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት ውስጥ የሥነ¬-ዜጋና የመራጮች ትምህርት መስጠት መሆኑ ይጠቀሳል። በዐዋጁም ላይ ቦርዱ ይኽንን ተግባሩን በክልልና በከተማ መስተዳድር ደረጃ በሚቋቋሙ የቦርዱ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች አማካኝነት እንደሚያከናውን በተገለጸው መሠረት፤ የቦርዱ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል በተለያዩ ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ከሚገኙ የቦርዱ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ጋር በመተባበር በየክልሉና ከተማ መስተዳድሮቹ ለሚገኙ የብሔራዊ ዩኒቨርስቲ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች፤ በሥነ-ዜጋና በመራጮች ትምህርት ዙሪያ ሥልጠና ሰጥቷል። በዚኽም አግባብ ቦርዱ ሥልጠናው ባልተሰጠባቸው ዩኒቨርስቲዎች ሥልጠናውን መስጠት ቀጥሎ፤ ለሰመራ ዩኒቨርሲቲ እና ለድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎች ሰጥቷል።

Share this post

የቦርዱ ውጤታማ የፕሮግራም በጀት አተገባበር እንዲጠናከር ለቦርዱ ኃላፊዎች የዐቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተለያዩ ሥራ ክፍሎቹ አማካኝነት ቦርዱ የተቋቋመለትን ዐላማ በብቃት መፈጸም የሚያስችለውን ሙያዊ ሥልጠና በተለያዩ ዘርፎች ላይ ሲያሰጥ ቆይቷል። ከዚኽም ጋር ተያይዞ የቦርዱን ስትራቴጂክ ዕቅድ ከመንግሥት የፕሮግራም በጀት ማዕቀፍ ጋር አቀናጅቶ የሚሠራበትን ውጤታማ የአሠራር ሥርዓት ላይ በቂ ግንዛቤ እንዲኖር ለማስቻል፤ በቦርዱ ዋና መሥሪያ ቤትና በክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶቹ ለሚሠሩ የሥራ ክፍል ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሙያዎች የአራት ቀናት የዐቅም ግንባታ ሥልጠና በኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዮት ባለሞያዎች አማካኝነት ሰጠ፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የኅትመት ውጤቶችን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አሠራጨ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና መራጮች ትምህርትን እንዲሁም የመራጮች መረጃን ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሠራ ይገኛል። ቦርዱ ትምህርቱን ተደራሽ ከሚያደርግባቸው ዘዴዎች አንዱ የተለያዩ የኅትመት ውጤቶችን በማዘጋጀት ለተለያዩ ተቋማትና ቤተ-መጽሓፍት ተደራሽ ማድረግ ነው።

Share this post