Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተማሪዎች የክርክር መድረክ በአዳማ ከተማ አካሔደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አንዱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እና የዜጎች ተሳትፎ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን ማዘጋጀት ዋነኛዉ ነዉ፡፡ በመሆኑም ቦርዱ ከላባ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ጋር በመተባበር፣ በአዳማ ከተማ ናፊያድ ት/ቤት በተግባር የተደገፈና ለተማሪዎች ግንዛቤን የሚያስጨብጥ የክርክር እና የምርጫ ናሙና ኹነት አካሒዷል፡፡ በመድረኩ የትምህርት ቤቱ አስተዳደር አካላትን ጨምሮ ወላጆች፣ መምህራን፣ ተማሪዎች፣ አካል ጉዳተኞች፣ ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የተዉጣጡ ጋዜጠኞች እና ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተሳትፈዋል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሐበጋር ዲቤትስ ጋር በመተባበር በሐረር ከተማ የክርክር መድረኮችን አዘጋጀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዜጎች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርጉ እና የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ላይ የሚኖራቸዉን ተሳትፎ ለማጉላት የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ቦርዱ ከሐበጋር ዲቤትስ (ደበበ ኃ/ገብርኤል የሕግ ቢሮ) ጋር በመተባበር በሐረር ኤስ ኦ ኤስ እና በሐረር ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተማሪዎች መካከል የክርክር መድረክ አካሄዷል፡፡

የክርክሩ ፍሬ ሀሳቦች በሁለት ርዕሰ-ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ሲሆን እነርሱም፡ ለኢትዮጵያ የሚሻለዉ የፖለቲካ ሥርዓት ፕሬዝዳንታዊ ወይስ ፓርላሜንታዊ እንዲሁም የነፃ ገበያ ሥርዓት ለኢትዮጵያ ዕድገት የተሻለ ሥርዓት ነዉ ወይስ አይደለም? የሚሉ ነበሩ፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ሥጋት አስተዳደርና የምርጫን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ማዕቀፍን የተመለከተ ዐውደ ጥናት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትላንት ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ.ም. የሥጋት አስተዳደርና የምርጫን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ማዕቀፍን የተመለከተ ዐውደ ጥናት አካሄደ። በዐውደ ጥናቱ ላይ የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ሜላት ወርቅ ኃይሉን ጨምሮ አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት የተገኙ ሲሆን፤ የቦርዱ የየሥራ ክፍል ኃላፊዎችም ተገኝተዋል። ዐውደ ጥናቱን የቦርድ አመራር አባሏ ብዙወርቅ ከተተ በንግግር የከፈቱት ሲሆን፤ በንግግራቸውም ዐውደ ጥናቱ በዋናነት ዓላማው ያደረገው ቦርዱ ከሣምንታት በፊት ያስተዋወቀውንና ቦርዱ እንደአዲስ ከተቋቋመ ወዲህ መጀመሪያ የሆነውን የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድን በመተግበር ሂደት የተለያዩ ተግዳሮቶች ቢገጥሙት እንዴት ባለ’አግባብ ሣይንሳዊ መንገድን ተከትለን መፍታት እንችላለን፤ በዚህም ሂደት ማን ምን ሚና አለው የሚለውን መገምገምና መለየት በማስፈለጉ እንደሆነ አብራርተዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሴፍ ላይት ኢኒሼቲቭ ጋር በመተባበር የወጣቶች የክርከር መድረክ አዘጋጀ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ስርዓት ዙሪያ የወጣቶች ተሳትፎን ለማጉላት ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ሰኔ 1 እና 8 ቀን 2016 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል በቢሾፍቱ እና ጅማ ከተሞች ቦርዱ ሴፍ ላይት ኢኒሼቲቭ ከተባለ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር ወጣቶች የተሳተፉበትን የክርክር መድረክ አካሔዷል፡፡ የክርክር መድረኩ መክፈቻ ፕሮግራም ሰኔ 1 ቀን 2016 ዓ.ም. በቢሾፍቱ ከተማ በርታ ደበሌ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን ቀጣይ መድረኩ ሰኔ 8 ቀን 2016 ዓ.ም. ጅማ ከተማ አሜሪካን ኮርነር የህዝብ ላይብረሪ ዉስጥ ተካሔዷል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ሶዶ እና አርባምንጭ ከተሞች የክርክር መድረክ አካሔደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እና የምርጫ ሂደቶች ዙሪያ ዜጎችን ለመድረስ ያስችለዉ ዘንድ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ቦርዱ ድሪም ፎር ዴቨሎፕመንት ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ከተባለ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፡ ወላይታ እና አርባ ምንጭ ከተሞች በተማሪዎች፣ አካል ጉዳተኞች እና ሴቶች መካከል ሶስት የክርክር መድረክ አካሂዷል፡፡ የክርክሩ ጭብጡም በሶስት ርዕሰ-ጉዳዮች ዙሪያ ላይ ያተኮረ ሲሆን እነርሱም፡ ለሀገር ህልዉና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ግዴታ ነዉ ወይስ አይደለም?፣ማህበረሰቡ ስለ አካል ጉዳተኞች ያለዉ የተዛባ አስተሳሰብ አካል ጉዳተኞች በምርጫ ዙሪያ እኩል ተሳትፎ እንዳይኖራቸዉ አድርጓል ወይስ አላደረገም?፣ ሴቶች በምርጫ ወቅት በመምረጥ ነው ወይስ በመመረጥ የተሻለ ተሳትፎ የሚኖራቸዉ? በሚሉ የመከራከሪያ ሀሳቦች ዙሪያ ነዉ፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተማሪዎች የክርክር መድረክ በድሬደዋ ከተማ አካሔደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕግ ከተሰጡት ኃላፊነቶች መካከል ዜጎች ስለ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ሂደቶች በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸዉ ማስቻል አንደኛዉ ነዉ፡፡ በመሆኑም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ከሐበጋር ዲቤትስ (ደበበ ኃ/ገብርኤል ከተባለ የሕግ ቢሮ) ጋር በመተባበር ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች በተወከሉ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች መሀከል የክርክር መድረክ በድሬደዋ ከተማ አካሄዷል፡፡ የክርክሩ ጭብጥም በሁለት ርዕሰ-ጉዳዮች ዙሪያ ላይ ያተኮረ ሲሆን፡ ለኢትዮጵያ የሚሻለዉ የመንግስት ሥርዓት ፌደራላዊ ወይስ አሃዳዊ? እና ዴሞክራሲ ተመራጭ የፖለቲካ ሥርዓት ነዉ ወይስ አይደለም? በሚሉ ሀሳቦች ዙሪያ ነዉ፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የወጣቶች የክርክር መድረክን አዘጋጀ

የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኮሚኒቲ ሰስተነብል ዴቬሎፕመንት ኤይድ ከተባለ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር በ 3 የተለያዩ ከተሞች ማለትም ወላይታ ሶዶ፥ ሆሳዕና እና ወልቂጤ የክርክር መድረክ አካሂዷል። ይህ የክርክር መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፥ በሆሳዕና ከተማ ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም በወልቂጤ ከተማ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተካሄደ ሲሆን የሕግ ትምህርት ቤት ተማሪዎች እና የዩኒቨርሲቲዎቹ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። ክርክሩም በዋናነት በምርጫ ፥ዲሞክራሲና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ሲሆን ተማሪዎች በንድፈ-ኃሳብ ደረጃ የተማሯቸውን ፅንሰ-ሀሳቦች ተግባራዊ እንዲያደርጉ እድል ያመቻቸ መድረክ መሆኑ ተጠቅሷል።

Share this post

ቦርዱ የ6ኛውን ሀገር አቀፍ ቀሪና የድጋሚ ምርጫ ውጤት ይፋ አድርጓል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቤንሻንጉል-ጉሙዝ፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ያካሄደውን የ6ኛው ዙር ሀገር አቀፍ ቀሪና የድጋሚ ምርጫ ውጤት ሰኔ 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል።

የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ በተጠቀሱት አራቱ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ 29 ምርጫ ክልሎች ስር በሚገኙ በ1218 ምርጫ ጣቢያዎች መካሄዱ የታወቀ ሲሆን ውጤት ይፋ በማድረጊያ መርኃ-ግብሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች (ተወካዮች)፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያቀረቡአቸው ዕጩዎች፣ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኃላፊዎችና ተወካዮች፣ የሚዲያ አካላት፣ የፌዴራልና የክልል የጸጥታ አካላት እና ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች ታዳሚ ነበሩ።

Share this post