Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የህትመት ውጤቶችን በአፋር ክልል ውስጥ ለሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አሰራጨ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስለምርጫ ሒደት እና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ዜጎች በቂ ግንዛቤን ያገኙ ዘንድ የተለያዩ ስልቶችን በመቀየስ መልዕክቶችን ተደራሽ ማድረግ ላይ እየሠራ ይገኛል፡፡ በዚህም መሠረት የቦርዱ የሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል በቦርዱ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኩል በአፋር ክልል ውስጥ ለሚገኙ የሰመራ፣ ሎግያ፣ አይሳ፣ ዱብቲ እና ሚሌ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም አሳይታ መምህራን እና ሰመራ ጤና ሳይንስ ኮሌጆች በአማርኛ እና በአፋርኛ ቋንቋዎች የተዘጋጁ አምስት የተለያዩ ይዘት ያላቸው ማለትም፤ የምርጫ ሒደት፣ ምርጫ በኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ ምን ዓይነት የምርጫ ሥርዓት ትከተላለች፣ ሰላማዊ ምርጫ በኢትዮጵያ፣ እና ዴሞክራሲ እና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በሚሉ ርዕሶች የተዘጋጁ በቁጥር 11900 ብሮሸሮች እና መጽሔቶችን አስረክቧል፡፡

Share this post

ቦርዱ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የምርጫ ተሳትፎ እንዲጎለብት እየሠራ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሁሉም የሀገራችን ዜጎች የፓለቲካ ተሳትፎ መብታቸው በተለይም የመመረጥና መምረጥ መብታቸው እንዲጎለብት አካታች የምርጫ ሥርዓትን ለማጠናከር ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል።

ይህንንም ዕውን ለማድረግ ቦርዱ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በምርጫ ሂደት የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ያላቸውን ፍላጎት እና የሚገጥሟቸውን ተግዳሮቶች በዳሰሳ ጥናት በመለየት ምቹ የምርጫ ከባቢ ለመፍጠር ኢስት አፍሪካ ከተባለ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በአማካሪ ድርጅትነት ቀጥሮ በማስጠናት ላይ ይገኛል።

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለታቀደው የዳሰሳ ጥናት አማካሪ ድርጅቱ የጥናቱን መነሻ ዕቅድ ሪፖርት ለቦርዱ ሥራ አመራር፣ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች፣ ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት በማቅረብ ዕቅዱን (Inception plan) የሚያጎለብቱ የሀሳብ ግብዓቶችን (ምክረ ሃሳቦችን) ሰብስቧል።

Share this post

የምርጫ ጣቢያዎችን በቴክኖሎጂ በተደገፈ የመልከዓ ምድር የመረጃ ሥርዓት (ጂ.አይ. ኤስ) ለማካለል ቦርዱ ከባለድርሻ አካላት ጋር መከረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሀገራችን የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎችን በቴክኖሎጂ በተደገፈ ሥርዓት በመልከዓ ምድር የመረጃ ሥርዓት (ጂ.አይ. ኤስ) ታግዞ ለማዘመን እንቅስቃሴ ጀምሯል።

በመጀመሪያ ዙር የምርጫ ጣቢያዎችን በመልከዓ ምድር የመረጃ ሥርዓት (ጂ.አይ. ኤስ) ለማካለል የታቀደው ሥራ በድሬደዋ ሁለት፣ በሐረሪ ሶስት፣ በሲዳማ አስራ ዘጠኝ እንዲሁም በደቡብ ኢትዮጵያ ሰባት የምርጫ ክልሎች ላይ እንደሚተገበር ታውቋል።

ይህንንም ተከትሎ በምክክር መድረኩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ፤የሐረር እና የሲዳማ ክልሎች እና የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የክልል አስተዳደር አካላት፤ የሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊዎች፤ የፖሊስ ኮሚሽነሮች እና የየክልሎቹ የምርጫ ላይዘን ኦፊሰሮች ታዳሚ ነበሩ::

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን የመረጃ ኃብቶች ለመጠበቅና ለመንከባከብ የሚያስችል ሥልጠና እየተሰጠ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ተቋማዊ ትውስታዎችን በመሰነድ ለትውልድ ማስተላለፍን ዓላማ ያደረገ ሥልጠና ከቦርዱ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ ባለሙያዎች እየሰጠ ነው፡፡

ዘመናዊ የመረጃ አስተዳደርና የመረጃ ኃብቶች ጥበቃና እንክብካቤን በተመለከተ ከየካቲት 3 - 14 ቀን 2017ዓ.ም. በሚሰጠው ሥልጠና ሠልጣኞች ከምርጫ ጋር የተያያዙ የመረጃ ኃብቶች እንዴት እንደሚሰበሰቡ፣ እንደሚደራጁ እና እንደሚጠበቁ ጠለቅ ያለ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ያስችላል ተብሏል፡፡

በሥልጠናው መክፈቻ መርሃ-ግብር ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የታሪክ ጥበቃ ክፍላችን የበርካታ ሠነዶች እና መዛግብት ባለቤት በመሆኑ ለአጥኚዎች እና ተመራማሪዎች ጥናትና ምርምር ዕምቅ አቅም ያለው እና ሀገራዊ ፋይዳ ያለው በመሆኑ ያሉንን መረጃዎች እና መዛግብት በአግባቡ አደራጅተን መጠበቅ ይገባናል ብለዋል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በማሻሻል ላይ ያለው ዐዋጅ ረቂቅን በሲቭል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና በመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች አስተቸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ "የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ ቁጥር ቁጥር 1162/2011" ላይ ያደረገውን የዐዋጅ ማሻሻያ በተመለከተ ባሳለፍነው ሣምንት ለሁለት ተከታታይ ቀናት ለፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ለመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች በማቅረብ ማስተቸቱ ይታወቃል። ቦርዱ ይኽን ከባለድርሻ አካላት ጋር በረቂቅ ዐዋጁ ላይ የሚያደርገውን ውይይት ቀጥሎ በተያዘው ሣምንትም ማለትም ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም. የረቂቅ ዐዋጅ ማሻሻያን ለሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶችና ለመገናኛ ብዙኃኑ አከላት ተወካዮች በማቅረብ ከተሣታፊዎቹ ሃሳብ አስተያየት ተቀብሏል።

Share this post