Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርት የስራ ክፍል ከቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት በክልሉ ከሚገኙ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር የወጣቶች የበጎ ፈቃድ ስልጠናን አስመልክቶ ምክክር አደረገ።

የቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት የሥራ ክፍል ባለሙያ በጋራ በመሆን በስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት ዙሪያ ከቦርዱ ጋር እየሰሩ ለሚገኙ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንዲሁም ከሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለተውጣጡ የተማሪ ተወካዮች ትምህርቱን በክልሉ ለሚገኙ ልዩ ልዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች በስፋት ማዳረስ ስለሚቻልበት ዘዴ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶቹ በበኩላቸው በሚቀጥለው ዓመት የሚደረገውን 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ታሳቢ ያደረገ እቅድ ነድፈው የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርትን በተጠናከረ መልኩ ለመስጠት ዝግጅት እንደሚያደርጉ የገለጹ ሲሆን የተማሪዎች ተወካዮች በበኩላቸው ትምህርቱን በየትምህርት ቤታቸው በሚገኙ ሚኒ ሚድያዎችና በየወቅቱ በሚደረጉ ሁነቶች ለተማሪዎች ለማሰራጨት ማቀዳቸውን ገልጸው ቦርዱ ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል። የቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የስነ ዜጋና መራጮች ትምህርት የስራ ክፍል ባለሙያ ትምህርቱን በዘላቂ

Share this post

የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የህትመት ውጤቶችን ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ለሚገኙ የትምህርት ተቋማት አስረከበ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ስራ ክፍል ዜጎች በምርጫ ሒደት እና በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዙሪያ ግንዛቤን ያገኙ ዘንድ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ትምህርቶች እና መረጃዎችን ተደራሽ ማድረግ ላይ እየሰራ ይገኛል። በዚህም መሰረት የስራ ክፍሉ በቦርዱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኩል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፤ ሆሣዕና ከተማ አሰተዳደር፣ ሀላባ ዞን፣ ሀድያ ዞን፣ ጉራጌ ዞን፣ ስልጤ ዞን እና፣ ከምባታ ዞን ውስጥ ለሚገኙ 30 የሁለተኛ ደረጃ እና መሠናዶ ትምህርት ቤቶች በአማርኛ ቋንቋ “ምርጫ በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ የተዘጋጁ በቁጥር 900 ቡክሌቶችን አስረክቧል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህጻናት ፓርላማ ምስረታ ሥልጠና እና ሙያዊ ድጋፍ ሰጠ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 102 መሰረት ምርጫን የማስፈጸም ሥልጣን የተጣለበት ገለልተኛ ተቋም ነው፡፡ በመሆኑም ዜጎች በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እና በምርጫ ሂደት ዙሪያ ግንዛቤን ያገኙ ዘንድ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ በዚህም መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህጻናት ፓርላማ ባካሄደው የምስረታ እና የሥራ አስፈጻሚዎች ምርጫ ላይ በቦርዱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኩል የምርጫ ኦፕሬሽን እና የሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍሎች ባለሙያዎች በምርጫ ሂደት እና በዴሞክራያዊ መብት ልምምድ ዙሪያ ሥልጠና ሰጥተዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የህትመት ውጤቶችን በሐረር ከተማና በአጎራባች የገጠር ከተሞች በሚገኙ የትምህርት ተቋማት አሰራጨ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ ዜጋና መራጮች ትምህርት የሥራ ክፍል ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ እና በዜጎች ተሳትፎ ዙሪያ የዜጎችን ግንዛቤ የሚያጎለብቱ መልእክቶችን የያዙ የህትመት ውጤቶችን ማዘጋጀትና ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ተደራሽ ማድረግ ነው። በዚህም መሰረት የሥራ ክፍሉ ከቦርዱ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት በአማርኛና በኦሮምኛ ቋንቋ የተዘጋጁ በቁጥር 2950 ቡክሌቶችን እንዲሁም 46 የብሬል ቡክሌቶችን በሐረር ከተማ ለሚገኙ የመንግስትና የግል ሁለተኛ ደረጃ ት/ት ቤቶች፣ ለከፍተኛ ት/ት ተቋማት፣ በአጎራባች የገጠር ወረዳ ለሚገኙ ት/ት ቤቶች እንዲሁም ለአንድ መስማትና ማየት የተሳናቸው ት/ቤት አሰራጭቷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተለየያዩ የኦሮሚያ ከተሞች ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች የስነ ዜጋና መራጮች ትምህርት ይዘት ያላቸው የህትመት ውጤቶችን አሰራጨ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት የሥራ ክፍል መራጮች በዕውቀት ላይ የተመሠረተ ምርጫ እንዲያካሂዱ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ ሂደት ዙሪያ የሚያጠነጥኑ የተለያዩ መልዕክቶችን የያዙ የህትመት ውጤቶች በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ የትምህርት ተቋማት እና የሕዝብ ቤተ-መጻሕፍት እያሰራጨ ተደራሽነቱን እያሰፋ ይገኛል። በዚህም ሂደት የሥራ ክፍሉ ከቦርዱ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመሆን በአማርኛና በኦሮምኛ ቋንቋ የተዘጋጁ በቁጥር 2160 የሚሆኑ በስነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ዙሪያ ያተኮሩ ብሮሸሮች፣ ቡክሌቶች፣ አዋጆች እንዲሁም የቦርዱ መልዕክት የታተመባቸው ቲሸርቶችን በኦሮሚያ ክልል በባቱና ሻሸመኔ ከተሞች በሚገኙ 18 ትምህርት ቤቶች ማሰራጨት ችሏል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሐረሪ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ፓርቲ ላይ መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም የሰጠው የእግድ ውሳኔ የተነሳ መሆኑን የወሰነበት ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሐረሪ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ፓርቲ ላይ መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም የሰጠው የእግድ ውሳኔ የተነሳ መሆኑን የወሰነበት ደብዳቤ ለማግኘት ኢዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የ7ኛው ጠቅላላ ሀገር አቀፍ ምርጫ የዕቅድ ዝግጅት ምክክር ተጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ ዕቅድ እና የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ዕቅድ ዝግጅት ላይ የቦርዱ ሥራ አመራር አባላት፣ የቦርዱ ሥራ ክፍል ኃላፊዎችና የክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የሥራ ክፍል ኃላፊዎች በታደሙበት አውደ ጥናት አካሄደ።

የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ዕቅድን ከወዲሁ ማዘጋጀት ያስፈለገበት ዓላማ ምርጫውን ሕጉ በሚፈቅደው የምርጫ የጊዜ ሠሌዳ ለማካሄድ ዕቅዱን ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመላክ ለምርጫ ማስፈፀሚያ ሥራው የታለመው በጀት በወቅቱ እንዲፀድቅ ለማስቻል ያለመ ነው።

የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንዳሉት በ2018 ዓ.ም ለምናካሂደው የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ዝርዝር፣ የሚለካ፣ ወጪ ቆጣቢ እና በጊዜ የተገደበ ብሎም ለእያንዳንዱ የምርጫ ተግባሮቻችን ምክንያታዊ እና ተጨባጭ በጀት ለማዘጋጀት ይህን አውደ ጥናት አዘጋጅተናል ብለዋል።

Share this post

ቦርዱ አካል ጉዳተኞች በቀጣይ ምርጫዎች ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዲኖራቸው የዳሰሳ ጥናት እያስጠና መሆኑ ተገለፀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አካል ጉዳተኞች በ6ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የነበራቸውን ተሳትፎና ውክልና ምን ይመስል እንደነበረ አማካሪ ድርጅት ቀጥሮ በማስጠናት ላይ ይገኛል።

የዳሰሳ ጥናቱ ዋነኛ ዓላማ እነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች የፓለቲካ ተሳትፎቸው ውስን እንዲሆን ያደረጓቸውን ችግሮች ነቅሶ በማውጣት በቀጣይ በሚኖሩ ምርጫዎች ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዲኖራቸው ቦርዱ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ምክረ ሃሳቦችን ለማመላከት ያለመ ነው።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የህትመት ውጤቶችን በሶማሌ ክልል ውስጥ ለሚገኙ የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አስረከበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ዜጎች በዕዉቀት ላይ የተመሠረተ ምርጫን እንዲያደርጉ እና የዜግነት መብት እና ኃላፊነታቸውን በመገንዘብ ንቁ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ያስችል ዘንድ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡

Share this post