የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ታግዶ የማይሰረዝበትን መከላከያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ የወሰነበት ደብዳቤ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ታግዶ የማይሰረዝበትን መከላከያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ የወሰነበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
መግቢያ፣
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ታግዶ የማይሰረዝበትን መከላከያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ የወሰነበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ ያደረገውን ጠቅላላ ጉባኤ ተቀብሎ ያፀደቀው መሆኑን የገለፀበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዱቤኔ ደጊኔ ነፃነት ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ውድቅ መደረጉን የወሰነበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1133/2011 በአንቀጽ 23 እና 24 መሠረት ቦርዱ በሁሉም የሀገራችን ክልሎች ምርጫ የሚያስተባብሩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች እንደሚያቋቁም ይደነግጋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባልተማከለ የምርጫ አስተዳዳር ሥርዓቱ (Decentralized electoral administration) በምርጫ ዑደት ውስጥ ከቅድመ ምርጫ አንሥቶ እስከ ድኅረ ምርጫ ሒደቶች ድረስ ያሉትን ክንዋኔዎች ለህዝብ ተደራሽ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት ይረዳው ዘንድ በቦርዱ ዋና መ/ቤት የሚገኝ ራሱን ችሎ የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን የሚያስተባብር የሥራ ክፍል አቋቁሟል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ድጋፍ በአማካሪ ተቋም ያስጠናውን በ 2013 ዓ.ም. ሀገራዊ ምርጫ ወቅት ሢሠራበት የነበረውን የሥነ ዜጋና መራጮች ትምህርት ማስተማሪያ ማንዋል የሲቪል ማኅበራት ድርጅት አመራሮች፣ ተወካዮች፣ የቦርዱ የፌደራል እና የክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊዎች እና የስነ-ዜጋና አካታችነት ባለሙያዎች በተገኙበት በመገምገም ሰነዱን የሚያዳብሩ ጠቃሚ ግብዓቶችን ሰበሰበ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 7 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፉ አድርጎ ያስጀመረውን የአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ስልታዊ ግቦች እና ዓላማዎች እንዲሳኩ በየደረጃው ያሉ የቦርዱ ሠራተኞችን ስለስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ይዘት እና አተገባበር ግንዛቤ እንዲኖራቸው የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች ተካሄዱ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአምስት ዓመቱ ስትራቴጂያዊ እቅድ ስኬታማነቱ የሚረጋገጠው እያንዳንዳችን የቦርዱ ሠራተኞች እና ኃላፊዎች በምናበረክተው ጉልህ አስተዋፅኦ ነው ያሉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ለስትራቴጂያዊ ዕቅዱ እውን መሆን አሁን እያሳያችሁት ያለውን ቁርጠኝነት አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ይጠበቃል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቴክኒክ ቡድን አዋቅሮ አንድ ዓመት በወሰደ ጊዜ ያስጠናውን የፆታዊ ትንኮሳ ፓሊሲ እና የማስተግበሪያ ሥነ-ሥርዓት (procedure) በፌደራል እና በክልል ለሚሰሩ የቦርዱ ጏላፊዎችና ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ አውደ ጥናት አስተዋወቀ።
በአውደ ጥናቱ በዋንኛነት የፆታዊ ትንኮሳ ፓሊሲ እና የማስተግበሪያ ሥነ-ሥርዓት አስፈላጊነት፣ የፆታዊ ትንኮሳ ባህሪያት እና መገለጫዎች፣ የፆታዊ ትንኮሳ ክስ የሚቀርብበት ሥነ-ሥርዓት፣ የፓሊሲው የተፈፃሚነት ወሰን እና ፆታዊ ትንኮሳ በሚያስከትለው ችግሮች ላይ ገለፃ ተሰጥቶ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮገራም /United Nations Development Program-UNDP /ለምርጫ ቦርድ በሚሰጠው የ(SEEDS2) ፕሮጀክት ድጋፍ እኤአ በ2025 ዓመት ሊሠሩ የታሰቡ ሥራዎችን ለማቀድ በተካሄደው አውደ ጥናት ላይ ከቦርዱ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡ የአውደ ጥናቱ ዋና ዓላማም የቦርዱ ሥራ ክፍሎች ከUNDP (SEEDS2)ፕሮጀክት የሚያገኟቸውን ድጋፎች ተከትሎ የሚሠሯቸውን ሥራዎች በተገቢው መንገድ እንዲያቅዱ ማስቻል እና የምርጫ ቦርድን የሥራ ዕቅድና የዕቅድ አፈፃፃም ተቋማዊ አቅምን ለማሳደግ ያለመ ነበር፡፡