በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ ሊደርስ የሚችል ጥቃትን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል የአሠራር ሥርዓት ሠነድ አፀደቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመከላከል የሚያስችል የአሠራር ሥርዓት (Standard Operating Procedure (SOP)) አፀደቀ። በአሠራር ሥርዓቱ ጥቃቱን በተመለከተ የትኞቹ ተቋማት ይመለከታቸዋል የሚለውን የባለድርሻ አካላት ልየታን ጭምር ያካተተ ሲሆን፤ ከነዚኽም ውስጥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙ`ኃን ባለሥልጣን፣ ለምርጫ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኅብረት፣ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እና የኢትዮጵያ ሴት የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ጥምረት ይጠቀሳሉ።