ቦርዱ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎች የፀጥታ ሁኔታን የሚከታተል ቡድንን ሥምሪትና ተግባራትን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎች የፀጥታ ሁኔታን የሚከታተል ቡድንን ሥምሪትና ተግባራትን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ። የውይይቱን የመክፈቻ ንግግር የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸውም ቦርዱ ቀደም ሲል ከመንግሥት የፀጥታ ተቋማ በመቀጠልም ከፖለቲካ ፓርቲዎች የተሰበሰበውን የፀጥታ ሁኔታ መረጃ መሠረት አድርጎ የተለያዩ ውይይቶችን ማካሄዱን አስታውሰው፤ የዚኽም ውይይት ዋና ዐላማ ቀደም ሲል የቀረቡ መረጃዎች መሬት ላይ ወርዶ በትክክል ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በመመልከት ሁኔታውን የሚመለከት የክትትል ቡድንን ሥምሪትና ተግባራት ላይ መወያየት በማስፈለጉ እንደሆነ ተናግረዋል።