Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የኅትመት ውጤቶችን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አሠራጨ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና መራጮች ትምህርትን እንዲሁም የመራጮች መረጃን ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሠራ ይገኛል። ቦርዱ ትምህርቱን ተደራሽ ከሚያደርግባቸው ዘዴዎች አንዱ የተለያዩ የኅትመት ውጤቶችን በማዘጋጀት ለተለያዩ ተቋማትና ቤተ-መጽሓፍት ተደራሽ ማድረግ ነው።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተጠናቀቀው ሣምንት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር ተወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ-መንግሥቱ ላይ በተቀመጠውና በቦርዱ ማቋቋሚያ ዐዋጀ ላይ በተደነገገው መሠረት ተጠሪነቱ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሆኑ ይታወቃል፤ በዚኽም መሠረት ቦርዱ በተጠናቀቀው ሣምንት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር ተወያይቷል። በውይይቱ ወቅትም ሁሉም የቦርድ አመራር አባላትና የጽ/ቤት ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፤ በቦርዱ የዕቅድ ዝግጅት፣ ክትትል፣ ግምገማና የመማማር ሥራ ክፍል ከፍተኛ ባለሞያ አማካኝነት ቦርዱ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እያደረገ ያለውን ዝግጅን ጨምሮ እስካሁን የሠራቸውንና በመሥራት ላይ ያላቸውን ዋና ዋና ተግባራት በዝርዝር ቀርቧል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫና ተያያዥ ጉዳዮችን የተመለከቱ የኅትመት ውጤቶችን በቤንሻንጉል-ጉሙዝ እና በአማራ ክልሎች አሠራጨ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዜጎች በሥነ-ዜጋና በመራጮች ትምህርት ዙሪያ ያላቸዉን ግንዛቤ ለማሳደግ ያግዛል ያላቸዉን ዘዴዎች በመጠቀም የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። በዚህም መሠረት የቦርዱ የሥነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ከቦርዱ የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ጋር በመቀናጀት በተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ ምርጫና ተያያዥ ጉዳዮችን የተመለከቱ የኅትመት ውጤቶችን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ ላይ በስፋት እየሠራ ይገኛል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት ዙሪያ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎችና ከተማ መስተዳደሮች በአካታችነት ለማዳረስ እንዲቻል በየክልሎቹና ከተማ መስተዳድሮቹ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በጎ-ፍቃደኛ የሆኑ ወጣቶችን በመመልመል የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን በመስጠት ሂደት ውስጥ ተሣታፊ እንዲሆኑ ዕቅድ ይዞ ለተግባራዊነቱ በትኩረት እየሠራ ይገኛል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ሥነ-ዘዴውን የተመለከተ ዐውደ-ጥናት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አማካሪ ድርጅት ቀጥሮ ያሠራው የቦርዱን የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ሥነ-ዘዴ የገመገመ መነሻ ጥናት መጠናቀቁን ተከትሎ ግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም. ባካሄደው ዐዋደ-ጥናት፤ የጥናቱን ሂደትና ግኝት እንዲሁም ጥናቱን ተከትሎ የተሰጠውን ምክረ-ሃሳብ በአማካሪ ድርጅቱ ባለሞያዎች አማካኝነት ዐውደ ጥናቱ ላይ ተሣታፊ ለነበሩት የቦርዱ አመራሮች፣ ለሚመለከታቸው የቦርዱ ሥራ ክፍሎችና ባለድርሻ አካላት አቅርቧል።

Share this post

የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሁለተኛ ዙር የምርጫ ጣቢያዎችን በዲጂታል ሲስተም የመመዝገብ ሥራ ማከናወን ጀመረ

የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንደ አዲስ ከተቋቋመበት 2011 ዓ.ም. አንሥቶ አንድ ሀገራዊ ምርጫ እና ሦስት ሕዝብ ውሣኔዎችን ማስፈጸሙ ይታወቃል። ቦርዱ በቀጣይም የ7ኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ ለማከናወን የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች አጋርነት መድረክ አስፈላጊነት ላይ ውይይት ተካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች (ሲ.ማ.ድ) ጋር የሚኖር የአጋርነት መድረክ አስፈላጊነት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ። ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ምርጫ ቦርድ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምርጫን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ለሚኖራቸው ተሣትፎ ዕውቅና ከመስጠት አንሥቶ አብሮ እስከመሥራት የደረሰ ግንኙነት እንዳለው አስታውሰው፤ ይኽም ሲሆን ሚናን በመለየት ተባብሮ መሥራቱ የምርጫን ነፃና ገለልተኛ እንዲሁም ዲሞክራሲያዊነቱን በማረጋገጥ ረገድ ከፍ ያለ አስተዋፅዖ ያለው በመሆኑ እንደሆነ ተናግረዋል። በዚኽም መድረክ ላይ ማኅበራቱ በምርጫ ትምህርትም ላይ ባላቸውም ተሣትፎ ይሁን እንደታዛቢ በሚኖራቸው ኃላፊነት መሻሻል የሚገባቸውን እየለዩ መሄድና የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።

Share this post

ቦርዱ የፓለቲካ ፓርቲዎችን አቅም ለመገንባት የፓለቲከኞችን የምርጫ ክህሎት ለማጎልበት ሥልጠና መስጠት ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከኔዘርላንድ የመድብለ ፓርቲ የዲሞክራሲ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከተለያዩ የፓለቲካ ፓርቲዎች ለተውጣጡ ፓለቲከኞች በምርጫ ክርክር ክህሎት ላይ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

የሥልጠናው ዋንኛ ዓላማ ፓለቲከኞች ለመራጩ የሚያቀርቡት ማኒፌስቶ (ፓሊሲዎችና ፕሮግራሞች) የህዝብ ቅቡልነት እንዲያገኙ የፓለቲከኞች የምርጫ ክርክር ክህሎትን ማሳደግ ላይ ያተኮረ ነው።

በምርጫ ክርክር አማካኝነት ተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች ለመራጩ ህዝብ በሚሰጡት አማራጭ የፓሊሲ አማራጮች ምክንያት መራጮች ዕውቀት ላይ ተመስርተው የሚበጃቸውን እንዲመርጡ ከማስቻሉ ባሻገር የዲሞክራሲ ተሳትፎ ባህልን ይጎለብታል።

Share this post