Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበጎ ፈቃደኝነት ለሚሠማሩ ወጣቶች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። ከነዚኽም ተግባራት አንዱ ዜጎች በዕውቀት ላይ የተመሠረት ምርጫን እንዲያደርጉ የሚያስችላቸውን የሥነ ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት መስጠት በዋንኛነት ይጠቀሳል። በመሆኑም የቦርዱ የሥነ ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ከቦርዱ የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ጋር በመተባበር አዲስ አበባ እና በድሬደዋ ከተማ መስተዳደሮችን ጨምሮ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ፣ በሐረሪ፣ በአፋር፣ በሶማሊ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ እና በሲዳማ ክልሎች በመራጮች ትምህርት እና በመረጃ ሥርጭት ዘመቻ ሥራዎች ላይ ለሚሣተፉ 775 በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች የሁለት ቀናት ሥልጠና ሰጥቷል።

Share this post

ቦርዱ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሲያደርግ የነበረውን ውይይት አጠናቀቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም. 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ሲያደርግ የነበረውን የሁለት ቀናት ውይይት አጠናቀቀ። ቦርዱ በመጀመሪያ ቀን ውይይቱ ሀገር ዐቀፍ ፖለቲካ ፓርቲዎችንና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን ከክልል ርዕሰ መስተዳድሮችና ከከተማ መስተዳድር ከንቲባዎች፣ ከፌደራልና ከክልል የፀጥታ ተቋማት አመራሮች ጋር ያወያየ ሲሆን፤ በሁለተኛው ቀን ውይይቱ ደግሞ የክልል ዐቀፍ ፖለቲካ ፓርቲዎችንና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን አወያይቷል።

Share this post

ቦርዱ የፖለቲካ ፓርቲ ሲሰተም አሰተዳዳሪዎች በቦርዱ ባለሙያዎች ድጋፍ እየተደረገላቸው ዕጩዎቻቸውን እንዲመዘግቡ ማድረግ ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዕጩዎች ምዝገባን በምርጫ የጊዜ ሠሌዳው መሠረት ከጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ ቀደም ሲል ባሳወቀው መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ሥርዓት ታግዘው በመመዝገብ ላይ ያሉ ሲሆን፤ ይኽንንም ለማከናወን እንዲችሉ የሲስተም አስተዳዳሪ ወኪሎቻቸውን ለቦርዱ አሳውቀው በሁለት ዙር ለአራት ቀናት ሥልጠና እንዲወስዱ አድርጓል። ሥልጠናውን ከመስጠት በተጨማሪ በስልክ እንዲሁም የሲስተም አስተዳዳሪዎችን ያካተተ “ቴሌግራም ግሩፕ” በመክፈትም በምዝገባ ወቅት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ማንኛውንም ጥያቄዎቻቸውን ሲያስተናግድ ቆይቷል። ቦርዱ በተለያዩ አማራጮች የሲስተም አስተዳዳሪዎቹ የሚያከናውኑትን የዕጩዎች ምዝገባ ሲያስተባብር የነበረ ሲሆን፤ ከዛሬ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም.

Share this post

ቦርዱ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመምረጥ የሚሳተፉበትን ምቹ መደላድል ለመፍጠር ያለመ ውይይት ከተቋማቱ አመራሮች ጋር አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ከትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች ጋር የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የመራጮች ምዝገባ እና ድምጽ አሰጣጥን በሚመለከት ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ውይይት አደረገ፡፡

ውይይቱ የተካሄደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ፣ የዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚዳንቶች፣ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እና የትምህርት ሚኒስቴር ተወካይ በተገኙበት ነው፡፡

የውይይቱ ዓላማ ከምርጫ ክልላቸው ርቀው በዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች ልዩ የምርጫ ጣቢያ ተዘጋጅቶላቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ያለመ ነው፡፡

Share this post

NEBE Inaugurates First of Its Kind Voter and Candidate Registration System

The National Election Board of Ethiopia (NEBE) inaugurated a groundbreaking voter and candidate registration system. In her opening speech at the inauguration, NEBE Chairperson Melatwork Hailu stated that the Board has been engaged in various activities to implement “Innovation and Technology,” among the six pillars of the five-year strategic plan. She emphasized that the January 5, 2026, inauguration marks the launch of an inclusive voter and candidate registration system.

Share this post

የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎች ቅጥር ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ለማከናወን በርካታ የቅድመ ምርጫ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል። በመሆኑም ቦርዱ ምርጫ የሚያስፈጽሙ ገለልተኛ የምርጫ ጣቢያ ሠራተኞችን በጊዜያዊነት ለመቅጠር ይፈልጋል።

በዚኽም መሠረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መሥፈርቶች የምታሟሉ በሁሉም ክልሎች ላይ “በምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚነት” ማገልገል የምትፈልጉ አመልካቾች በሙሉ፤ ተከታዩን ማስፈንጠሪያ https://nebe-election.org/recruitment በመጠቀም ከታኅሣሥ 19 እስከ ታኅሣሥ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት እንድትመዘገቡ ቦርዱ ያሳውቃል። የምልመላ መሥፈርት፡-

የዕጩ ምዝገባን በተመለከተ የተሰጠ ማብራሪያ

ቦርዱ ኅዳር 8 ቀን 2018 ዓ.ም. በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ባስተላለፈው ጥሪ፤ ፖለቲካ ፓርቲዎች “ቦርዱ ያበለጸገውን ሲስተም” ተጠቅመው ዕጩዎቻቸውን ለመመዝገብ እንዲችሉ “በቅድሚያ” ከጥሪው ጋር የተያያዙትን ቅጾች በመጠቀም የተጠየቁትን መረጃዎች አሟልተው ለቦርዱ እንዲያቀርቡ ጥሪ ማስተላለፉ ይታወቃል።

የዕጩ ምዝገባ የሚከናወንበት አግባብ እና የቅጾች አጠቃቀም

1. የፖለቲካ ፓርቲ ቦርዱ ያበለጸገውን የዕጩ መመዝገቢያ ሲስተም ተጠቅሞ ዕጩ ለመመዝገብ በዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 እና የዕጩ ምዝገባ መመሪያ መሠረት በቅድሚያ የዕጩ ዝርዝር ማቅረቢያ ቅጽ አምስትን በመጠቀም የዕጩዎችን ዝርዝር መረጃ፤ የፓርቲውን ሊቀ-መንበር ሦስት የፊርማ ናሙና እና የመወዳደሪያ ምልክቱን ለቦርዱ አስቀድሞ ባሳወቀው ወኪል አማካኝነት ከኅዳር 8 እስከ ኅዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም. ለቦርዱ በአካል ማቅረብ ይኖርበታል፡፡