Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

ቦርዱ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት ይፋ ባደረገበት መድረክ ላይ ፓርቲዎች የምርጫ ሥነ-ምግባር ደንብ ፈረሙ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባሳለፍነው ሣምንት መጠናቀቂያ ባዘጋጀው መድረክ ላይ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ሥነ-ምግባር ደንብ ፈረሙ። ፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት ተወካዮች እንዲሁም መገናኛ ብዙ`ኃን በተገኙበት፤ 48 ፖለቲካ ፓርቲዎች ለምርጫ የሚወዳደሩባቸውን ምልክቶች ይፋ ለማድረግ የተዘጋጀውን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ቦርዱ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት ይፋ እስከሚያደርግበት ጊዜ ድረስ በነበረው የቅድመ-ምርጫ ተግባራቱ ምን ሲያከናውን እንደነበር ማብራሪያ ሰጥተዋል። የሥነ-ምግባር ደንቡን አስፈላጊነት አስመልክቶ ባደረጉት ንግግርም ምርጫ ነፃ፣ ሰላማዊና ፍትሐዊ ሆኖ የሚከናወነው ሁሉም ፓርቲ ሕግን አክብሮ ኃላፊነቱን ሲወጣ እንደሆነ፤ የምርጫው ስኬትም የሚረጋገጠውም ቦርዱ ለብቻው በሚያደርገው ጥረት ሣይሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት ዕኩል ኃላፊነቱን መወጣት ሲችል እንደሆነ በአጽንዖት ተናግረዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዋና አሠልጣኞች ሥልጠና መስጠት ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመሥክ አሠልጣኞችን በተዋረድ ለሚያሠለጥኑ ዋና አሠልጣኞች ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሥልጠና መስጠት ጀመረ። በትላንትናው ዕለት የካቲት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. የጀመረውንና በዛሬው ዕለት የሚጠናቀቀውን ሥልጠና የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በመክፈቻ ንግግራቸው፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊ እና ገለልተኛ እንዲሆን የምርጫ አስፈጻሚዎች ሚና የማይተካ በመሆኑ፤ ብቁ እና በሕግ መሠረት የሚሠሩ ምርጫ አስፈጻሚዎችን ለማብቃት የዋና አሠልጣኞች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን፤ ዋና አሠልጣኞቹ በሁለቱ ቀናት የሚያገኙትን ሥልጠና በትኩረትና በኃላፊነት ስሜት ለመሥክ አሠልጣኞች ማስተላለፍ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።

Share this post

ቦርዱ ሐሰተኛና አደናጋሪ ምርጫ ነክ መረጃዎችን ለመከላከል የሚያስችለውን ብሔራዊ ትብብር ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በያዝነው ሣምንት በምርጫ እና በድኅረ ምርጫ ወቅት ሊፈጠሩ የሚችሉ ምርጫ ነክ ሐሰተኛና አደናጋሪ መረጃዎችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የሚያስችለውን የብሔራዊ ትብብር ስምምነት ይፋ አደረገ። የይፋ ማድረጊያው መድረኩን የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በንግግር የከፈቱት ሲሆን፤ በንግግራቸውም የትብብር ማዕቀፉ ቦርዱ መጪው ምርጫ ነፃ እና ተዓማኒ እንዲሆን ምርጫ ነክ መረጃዎች ተዛብተው እና አሳሳች ሆነው ለኀብረተሰቡ እንዳይቀርቡና 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተዓማኒነት ተጠብቆ እንዲከናወን ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራበት ነው ብለዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሣተፉ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መስጠት ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመራጮች ትምህርት ላይ ለሚሣተፉ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መስጠት ጀመረ። ከዛሬ የካቲት 11 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚቆየውን ሥልጠና የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቦርዱ የሥራ አመራር አባል የሆኑት ተኽሊት ይመስል ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም የሲቪልና የመራጮች ትምህርት የአንድ ጊዜ ሥራ አለመሆኑን ተናግረው፤ የመራጮች ምዝገባ ሊጀምር ጥቂት ቀን እንደመቅረቱ መጠን ትኩረታችንን በመራጮች ትምህርት ላይ በማድረግ፤ መራጩ ሕዝብ የመራጭነት ካርዱን ከየካቲት 28 እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚከናወነው የመራጮች ምዝገባ ወቅቱን ጠብቀው ካርድ እንዲወስዱና በምርጫ ቀንም እንዲሁ በዕውቀት ላይ ተመሥርተው ድምፅ እንዲሰጡ የሚያስችላቸውን ትምህርት መስጠት እንደሚገባ ተናግረል። ቦርድ የመራጮች ትምህርት ለመስጠት የሚያስችለውን ማንዋል አሻሽሎ እንዳቀረበና ማኅበራቱም ትምህርቱን በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት እንደሚሰጡ ያላቸውን ዕምነት ገልጸዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቦ.ዴ.ፓ) በሚመለከት ያወጣዉ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ-መንግሥቱና በምርጫ ሕጉ መሠረት ከተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት አንዱ የፖለቲካ ድርጅቶችን መመዝገብ፣ መከታተልና መቆጣጠር እንደሆነ ይታወቃል፡፡

በዚህም መሠረት የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቦ.ዴ.ፓ) ሊቀ-መንበር ታኅሣሥ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. በቁጥር ቦሮ 2135 /2018 በተጻፈ ደብዳቤ የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ጥር 22 ቀን 2012 ዓ.ም. ክልላዊ ፓርቲ ሆኖ እንዲንቀሳቀስ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠው የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ ዕውቅና እንዲሠረዝ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔ ኅዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ የወሠነ መሆኑን አሳውቆ፤ ቦርዱ በውሣኔው መሠረት ፓርቲውን ከምዝገባ እንዲሠርዝ በማለት አመልክቷል ።

በመሆኑ የፓርቲውን መሠረዝ አስመልክቶ ተቃውሞ ያለው ሰው ከነገ የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በ14 ቀናት ውስጥ ተቃውሞውን ለቦርዱ ጽሕፈት ቤት እንዲያቀርብ ቦርዱ ያስታውቃል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበጎ ፈቃደኝነት ለሚሠማሩ ወጣቶች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። ከነዚኽም ተግባራት አንዱ ዜጎች በዕውቀት ላይ የተመሠረት ምርጫን እንዲያደርጉ የሚያስችላቸውን የሥነ ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት መስጠት በዋንኛነት ይጠቀሳል። በመሆኑም የቦርዱ የሥነ ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ከቦርዱ የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ጋር በመተባበር አዲስ አበባ እና በድሬደዋ ከተማ መስተዳደሮችን ጨምሮ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ፣ በሐረሪ፣ በአፋር፣ በሶማሊ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ እና በሲዳማ ክልሎች በመራጮች ትምህርት እና በመረጃ ሥርጭት ዘመቻ ሥራዎች ላይ ለሚሣተፉ 775 በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች የሁለት ቀናት ሥልጠና ሰጥቷል።

Share this post

ቦርዱ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሲያደርግ የነበረውን ውይይት አጠናቀቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም. 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ሲያደርግ የነበረውን የሁለት ቀናት ውይይት አጠናቀቀ። ቦርዱ በመጀመሪያ ቀን ውይይቱ ሀገር ዐቀፍ ፖለቲካ ፓርቲዎችንና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን ከክልል ርዕሰ መስተዳድሮችና ከከተማ መስተዳድር ከንቲባዎች፣ ከፌደራልና ከክልል የፀጥታ ተቋማት አመራሮች ጋር ያወያየ ሲሆን፤ በሁለተኛው ቀን ውይይቱ ደግሞ የክልል ዐቀፍ ፖለቲካ ፓርቲዎችንና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን አወያይቷል።

Share this post

ቦርዱ የፖለቲካ ፓርቲ ሲሰተም አሰተዳዳሪዎች በቦርዱ ባለሙያዎች ድጋፍ እየተደረገላቸው ዕጩዎቻቸውን እንዲመዘግቡ ማድረግ ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዕጩዎች ምዝገባን በምርጫ የጊዜ ሠሌዳው መሠረት ከጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ ቀደም ሲል ባሳወቀው መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ሥርዓት ታግዘው በመመዝገብ ላይ ያሉ ሲሆን፤ ይኽንንም ለማከናወን እንዲችሉ የሲስተም አስተዳዳሪ ወኪሎቻቸውን ለቦርዱ አሳውቀው በሁለት ዙር ለአራት ቀናት ሥልጠና እንዲወስዱ አድርጓል። ሥልጠናውን ከመስጠት በተጨማሪ በስልክ እንዲሁም የሲስተም አስተዳዳሪዎችን ያካተተ “ቴሌግራም ግሩፕ” በመክፈትም በምዝገባ ወቅት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ማንኛውንም ጥያቄዎቻቸውን ሲያስተናግድ ቆይቷል። ቦርዱ በተለያዩ አማራጮች የሲስተም አስተዳዳሪዎቹ የሚያከናውኑትን የዕጩዎች ምዝገባ ሲያስተባብር የነበረ ሲሆን፤ ከዛሬ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም.

Share this post