Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

NEBE Awarded 21st International Electoral Award

The National Election Board of Ethiopia (NEBE) was awarded the Electoral Ergonomic Award at the prestigious 21st International Electoral Awards and Symposium, a landmark gathering of global electoral leaders dedicated to advancing democratic excellence and sharing best practices. This event was hosted by the Independent Electoral Commission (IEC) of Botswana in partnership with the International Centre for Parliamentary Studies (ICPS).

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሴት ፖለቲከኞች በ7 ኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚኖራቸውን ተሣትፎ ለማሳደግ የሚያስችል የዐቅም ግንባታ ሥልጠና ሠጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተቋማዊ ኃላፊነቱን ሲወጣ ትኩረት ከሚሰጣቸው ተግባራት አንዱ የሥርዓተ-ፆታና ማኅበራዊ አካታችነት ተጠቃሽ ነው። ቦርዱ ሴት ፖለቲከኞች በ7 ኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚኖራቸውን ተሣትፎ ለማሳደግ በማሰብ መስከረም 19-20 ቀን 2018 ዓ.ም. የዐቅም ግንባታ ሥልጠና ሠጠ፡፡ የመድረኩን መክፈቻ ንግግር የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸውም ቦርዱ ሴቶችና እና አካል ጉዳተኞች በምርጫ ላይ የነቃ ተሣትፎና የጎላ ድርሻ እንዲኖራቸው የሚያበረታቱ ድንጋጌዎች በሕግ-ማዕቀፎቹ እንዲካተቱ ከማድረግ ባሻገር፤ በርካታ የዐቅም ግንባታ ሥልጠናዎችንና ድጋፎችን እየሰጠ እንደሚገኝ አስታውሰው፤ ይህም ሥልጠና በ7 ኛው ሀገራዊ ምርጫ የነቃ ተሣትፎ እንዲኖራቸው እንደሚያስችል ያላቸውን ዕምንት ገልጸዋል።

Share this post

ቦርዱ ዲጂታል የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባ ረቂቅ መመሪያዎች ላይ ከፓለቲካ ፖርቲዎች እንዲሁም ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ተወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተያዘው ዓመት በሚያካሂደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ከሚያስተዋውቃቸው ዘመናዊ የምርጫ ሥርዓት ውስጥ አንዱ መራጮችና ዕጩዎች ኢንፍራስትራክቸር ባሉባቸው ቦታዎች በመሆን ራሳቸውን በራሳቸው በመራጭነት አልያም በዕጩነት እንዲመዘግቡ የሚያስችል የዲጂታል አማራጮች እንደሆኑ ይታወቃል። ቀደም ሲል ቦርዱ ያበለጸገውን በቴክኖሎጂ የታገዘ የመመዝገቢያ ሥርዓት ምን ዓይነት ሂደትን እንደሚከተል የአተገባበር ቅደም ተከተሉን ለፖለቲካ ፓርቲዎችና ለሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች በማሳየት ግብዓት የሰበሰበ ሲሆን፤ ሥራውን ለመሥራት የሚያስችለውን የተሻሻለውን ዐዋጅ ተከትሎም መመሪያ ማውጣት በማስፈለጉ ባሳለፍነው ሣምንት መስከረም 9 እና 10 ቀን 2018 ዓ.ም. ከፓለቲካ ፖርቲ ተወካዮች እንዲሁም ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች ጋር አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት በተገኙበት ምክረ-ሐሳብ መሰብሰቢያ ውይይት አኳሂዷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሥነ-ዜጋ እና ለመራጮች ትምህርት ክፍል ባለሙያዎቹ የዐቅም ግንባታ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ በ2018 የሚያስፈጽመው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ እያከናወናቸው ከሚገኙ በርካታ ተግባራት ውስጥ የቦርዱን ባለሞያዎች ዐቅም የሚያጎለብቱ ሥልጠናዎችን መስጠት ይጠቀሳል። ቦርዱ ነሐሴ 28-29 ቀን 2017 ዓ.ም. ለዋናው መሥሪያ ቤትና ለቅርንጫፍ ጽ/ቤቶቹ የሥነ-ዜጋ እና የመራጮች ትምህረት ሥራ ክፍል ባለሞያዎቹ ሥልጠና ሰጠ። የሥልጠናውን የመክፈቻ ንግግር የቦርድ አመራር አባል የሆኑት ተክሊት ይመስል ያደረጉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም የሥልጣን ባለቤት ሕዝብ መሆኑን አስታውሰው የመራጮች ትምህርት መስጠቱም፤ የሥልጣን ባለቤት የሆነው ሕዝብ አስፈላጊው ግንዛቤ ኖሮት እንዲመርጥ እንደሚያስችለው ተናግረዋል። ይኽም ሲሆን በሥልጠናዎቹ አካታች መሆን መሠረታዊ ነገርና የግድ የሚል እንደሆነ አስገንዝበዋል።

Share this post

ቦርዱ በክርክር ክኅሎት ልምምድ ምንነት እና አተጋባበር ላይ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮቸን ያሣተፈ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይ በፓለቲካ ፖርቲዎች መካከል የሚካሄደው የፖሊሲ አማራጮ ክርክርን ታሳቢ ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮችን ባሣተፈ መልኩ በትላንትናው ዕለት ነሐሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም. አካሄደ። ፖለቲካ ፓርቲዎች ሳይንሳዊ መንገድን ተከትለው ለመራጩ ሕዝብ ፖሊሲዎቻቸውንና ፕሮግራሞቻቸውን እንዴት ባለ ሁኔታ ማቅረብ እንዳለባቸው ግንዛቤ ማስጨበጥ ዐላማው ያደረገውን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም መራጩ ሕዝብ በዕውቀት ላይ ተመሥርቶ እንዲወሥንና ድምፅ እንዲሰጥ ለማስቻል የመራጮች ትምህርትና የምርጫ ቅስቀሳ ማድረግ እንደሚያስፈልገው ሁሉ፤ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሚደረጉ ፖሊሲና ፕሮግራማቸውን የተመለከቱ ክርክሮችም እንዲሁ ወሣኝነት እንዳላቸው ተናግረዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፓለቲካ ፖርቲዎችን የውስጥ አለመግባባት አፈታት ሥርዓታቸውን ለማጎልበት የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፓለቲካ ፖርቲዎች የውስጥ አለመግባባት አፈታት ስርዓታቸውን አጠናክረው እንዲተገብሩ የሚስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

መልካም አስተዳደርን ለማጎልበት እና የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደትን ለማጠናከር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡ ከነዚህም መካከል የፓለቲካ ፓርቲዎችን አቅም ማጎልበት ይገኝበታል፡፡ የስልጠናው ዋንኛ ዓላማ ፖለቲካ ፓርቲዎች የውስጥ አለመግባባቶችን የሚፈቱበት ዘላቂነት ያለው ጠንካራ አደረጃጀት እና ሥርዓት ፈጥረው አለመግባባቶችን በውስጥ አቅማቸው ለመፍታት እንዲችሉ ለማድረግ ነው፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን የተመለከተ የማኅበረሰብ ቲያትር በአዲስ አበባ ከተማ አቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን የተመለከተ የማኅበረሰብ ቲያትር በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙት በኮከበ ጽባሕ እና በከፍተኛ 12 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች፤ እንዲሁም “በጃንሜዳ የስፖርትና የሥልጠና ማዕክል” እና በመዲናዋ ከፍተኛ የሕዝብ እንቅስቃሴ ከሚበዛባቸው አካባቢዎች አንዱ በሆነው በመገናኛ አካባቢ አቀረበ።

በከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ ውስጥ በቀረበው ቲያትር ላይ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል የሚገኙ ተማሪዎች፣ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች የተገኙ ሲሆን፤ በቲያትሩም ላይ ስለምርጫ ሥነ-ባህሪያት፣ ስለመሠረታዊ የዴሞክራሲ ጽንሰ-ሐሳብና መርኆዎች፣ ስለማኅበራዊ አካታችነትና አካል ጉዳተኝነት ዲሞክራሲ ለዜጎች የሚያስገኘውን መብት ተግባራዊ ከማድረግ ሊገድበን እንደማይገባ እያዝናና የሚያስተምር መልዕክት ተላልፎበታል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን የተመለከተ የማኅበረሰብ ቲያትር በባህርዳር ከተማ አቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ “አሣታፊ የማኅበረሰብ ቲያትር ለአካታች የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት” በሚል ርዕስ በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ፓፒረስ አደባባይ (ሰንበት ገበያ) ላይ ቲያትር አቀረበ። በኪነ-ጥበብ ሥራው ላይ ሥርዓተ ፆታና ማኅበራዊ አካታችነትን፣ ሐሰተኛ መረጃን መከላከልና ኃቅን ማጣራትን፣ የዜጎች መብቶችና ግዴታዎችን፣ ሰላማዊ የግጭት አፈታትን፣ የእያንዳንዱ ዜጋ የምርጫ ተሣትፎና የድምፅ ዋጋን የተመለከቱ የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክቶች ተላልፈውበታል።

ቦርዱ ከአማራ ክልል “ፎቶ’ግራፈር እና ቪዲዮ’ግራፈር ባለሙያዎች ማኅበር” ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሕዝብን እያዝናኑ ግንዛቤ የማስጨበጫ የኪነ-ጥበብ ሥራ በቀጣይ በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች የሚካሄድ ይሆናል።

Share this post