Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለቀጣዮ አገር አቀፍ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ሰነዶች ህትመትና የቁሳቁሶች ግዥ ጀመረ

ታኅሣሥ 9 ቀን 2012 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለቀጣዩ አገራዊ ምርጫ ከሚያደርጋቸው ዝግጅቶች መካከል አንዱ የሆነውን የመራጮች ምዝገባን ዘመናዊ እና ተአማኒ የሚያደርግ የህትመት ሥራ እንዲጀመር በትላንትናው  ዕለት በዱባይ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
የዚህ የህትመት ውል ዓላማ የምርጫው ሂደት ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ እና አዲሱ የምርጫ ህግ ላይ የተቀመጡትን መስፈርቶች ያሟላ እንዲሆን፣ ሊፈጠሩ የሚችሉ ስህተቶችን ለመቀነስና እና ማጭበርበርን ለማስወገድ የሚረዳ እንዲሆን እንዲሁም ለምርጫ አስፈጻሚዎች ለመረዳትና ለማስፈጸም ቀላል እንዲሆን ለማድረግ ነው፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሚከተሉት በምዝገባ ሂደት ላይ የነበሩ ፓርቲዎች እውቅና ሰጠ

ታኅሣሥ 2 ቀን 2012 ዓ.ም.

ማብራሪያ

ሰርተፍኬት የተሰጣቸው ፓርቲዎች እውቅናቸውን ያገኙት በቀድሞው አዋጅ 537/2001 ዓ.ም. መስፈርቱን ጨርሰው አሟልተው ውሳኔ ሲጠብቁ የነበሩ ሲሆን በአዲሱ አዋጅ መሠረት መሟላት ያለበትን መስፈርት እንደማንኛውም ፓርቲ በቦርዱ መመሪያ መሠረት የሚያሟሉ ይሆናል፡፡

Share this post

የመረጃ ማስተካከያ

ኅዳር 30 ቀን 2012 ዓ.ም.                             

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀጣዩ አገር አቀፍ ምርጫ የሚካሄድበትን ቀን አሳወቀ በሚል በተለያዩ ሚዲያዎች እየታየ ያለው ዘገባ ከእውነት የራቀ ሲሆን ቦርዱ አገራዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ቀን እና ጊዜ ሰሌዳ አዘጋጅቶ ሲጨርስ የሚያሳውቅ ሲሆን ዜጎች ከቦርዱ ኢፌሴላዊ መግለጫ ውጪ የሚወጡ ሪፓርቶችን እና “ውስጥ አዋቂ መረጃዎችን” ችላ እንዲሉ ቦርዱ ያሳስባል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post

የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔ የመጨረሻ ውጤት

ኅዳር 24 2012  

የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔ የመጨረሻ ውጤት 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔን በኅዳር 10 ቀን 2012 ዓ.ም. ያስፈጸመ ሲሆን ኅዳር 13 ቀን 2012 ዓ.ም. የመጀመሪያ ደረጃ ውጤት ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ ቦርዱ ከመጀመሪያ ደረጃው ውጤት በማስከተል የእያንዳንዱን የምርጫ ጣቢያዎች ውጤት በዝርዝር በመገምገም፣ የድምር እንዲሁም ሌሎች የምርጫ ውጤት አለመጣጣም (discrepancies) ያለባቸውን ጣቢያዎች በማየት ውሳኔ አስተላልፎ የሚከተለውን የመጨረሻ ውጤት አሳውቋል፡፡ በመሆኑም በአጠቃላይ ድምፅ ከተሰጠባቸው 1,692 ምርጫ ጣቢያዎች እና ተጨማሪ 169 ድምፅ መስጫ ጣቢያዎች መካከል በ235 የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ቦርዱ የተለያዩ የድምርና የውጤት አለመጣጣም ችግሮች (discrepancies) አግኝቷል፡፡

Share this post

ህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚነት ስለመመዝገብ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሲዳማ ህዝበ ውሳኔ አፈጻጸም ሂደት፣ በህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚነት የሰራችሁ እና የአዲስ አበባ መስተዳድር ፕብሊክ ሰርቪስ ያወጣውን መስፈርት የምታሟሉ በምርጫ ማስፈጸም ስራችሁ ምክንያት ብቻ የጊዜ ገደብ ያለፈባችሁ አስፈጻሚዎች

1. የአስፈጻሚነት ባጃችሁን
2. የ2010 ዓ.ም እና 2011 ዓ.ም ተመራቂነታችሁን የሚያሳይ የትምህርት ማስረጃችሁን
3. የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪነት መታወቂያ በመያዝ

ህዳር 17 እና 18 ቀን 2012 ዓ.ም ሳሪስ በሚገኘው የቦርዱ ማሰልጠኛ ማእከል በመገኘት መመዝገብ እንደምትችሉ እናሳውቃለን፡፡ ቦርዱ በነዚህ ሁለት ቀናት የተመዘገቡ አስፈጻሚዎችን ስም ዝርዝር ለአዲስ አበባ ፕብሊክ ሰርቪስ ቢሮ የሚያስተላልፍ ሲሆን በነዚህ ቀናት ያልተመዘገቡ አስፈጻሚዎችን ስም ለመላክ እንደማይገደደድ ለማሳሰብ ይወዳል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የተዛባ መረጃ ማስተካከያ

ኅዳር 8 ቀን 2012 ዓ.ም.   

ዋልታ ኢንፎርሜሽን ዛሬ ጠዋት በሠራው ዘገባ የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባ የከተማው ነዋሪ 90 በመቶ ሻፌታን መምረጡ ተረጋገጠ በሚል የሠራው ዘገባ የተሳሳተ መረጃ ሲሆን ምክትል ከንቲባው የመራጮችን ተሳትፎንና ጸጥታን እንጂ የሕዝበ ውሳኔውን ውጤት የሚመለከት ምንም ዓይነት መግለጫ አልሰጡም። የምርጫ ውጤትን ማሳወቅ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኃላፊነት ብቻ መሆኑ እየታወቀ የሚዲያ አካላት የምርጫን ዓይነት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልጉ ዜናዎች ሲሠሩ ከፍተኛ ጥንቃቄ እና ትኩረት እንዲያደርጉ እንዲህ ዓይነት የተሳሳቱ መረጃዎች ሰላምንና ደህንነት የሚያናጉ በመሆናቸው እና በወንጀልም ስለሚያስጠይቁ ጋዜጠኞች ከዚህ ዓይነት ተግባራት እንዲቆጠቡ ቦርዱ ያሳስባል። 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 

Share this post

የተሳሳተ መረጃ ጥቆማ

ኅዳር 8 ቀን 2012 ዓ.ም.   

ዋልታ ኢንፎርሜሽን ዛሬ ጠዋት በሠራው ዘገባ የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባ የከተማው ነዋሪ 90 በመቶ ሻፌታን መምረጡ ተረጋገጠ በሚል የሀራው ዘገባ የተሳሳተ መረጃ ሲሆን ምክትል ከንቲባው የመራጮችን ተሳትፎንና ጸጥታን እንጂ የሕዝበ ውሳኔውን ውጤት የሚመለከት ምንም ዓይነት መግለጫ አልሰጡም፡፡

የምርጫ ውጤትን ማሳወቅ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኃላፊነት ብቻ መሆኑ እየታወቀ የሚዲያ አካላት የምርጫን ዓይነት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልጉ ዜናዎች ሲሠሩ ከፍተኛ ጥንቃቄ እና ትኩረት እንዲያደርጉ እንዲህ ዓይነት የተሳሳቱ መረጃዎች ሰላምንና ደህንነት የሚያናጉ በመሆናቸው እና በወንጀልም ስለሚያስጠይቁ ጋዜጠኞች ከዚህ ዓይነት ተግባራት እንዲቆጠቡ ቦርዱ ያሳስባል፡፡

Share this post

ለሚዲያዎች በሙሉ የተደረገ ጥሪ

ኅዳር 7 ቀን 2012 ዓ.ም.   

ለሚዲያዎች በሙሉ የዛሬውን ሕዝበ ውሳኔ አስመልክቶ አጭር ማብራሪያ ከምሽቱ 1 ሰዓት ላይ በጊዜያዊው ማስተባበሪያ ስለሚሰጥ እንድትገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post