Skip to main content

የተከበራችሁ የሚዲያ አካላት በሙሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛው ሀገር ዐቀፍ ምርጫን ለመዘገብ ፍላጎት ላላቸው ብዙኃን መገናኛ አካላት ጥሪ አድርጎና በደንቡ የተደነገጉትን ቅድመ ሁኔታዎችን ቅጽ በማስሞላት የዘገባ ባጅ በፍላጎታቸው ልክ እና በተለያየ ጊዜ መስጠቱ ይታወቃል። ይህም የዘገባ ባጅ የ6ኛው ሀገር ዐቀፍ ምርጫ እስኪጠናቀቅ ድረስ እንደሚያገለግልና በምርጫ ወቅትም ከምርጫ ጣቢያዎች በ200ሜ ዙሪያ ተገኝቶ ለመዘገብ የግድ የሚያስፈልግ መሆኑን በቦርዱ የማኅበራዊ ትሥሥር ገጾች ከመግለጽ ባሻገር፤ በህግ የተደነገገ መስፈርት ነው።

ለፓለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ

መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም በሶማሌ፣ በሐረሪ እና በደ/ብ/ብ/ህ ክልል ለሚከናወነው ድምፅ አሰጣጥ ሂደት የፓርቲ ወኪሎችን ባጅ ከምትወዳደሩበት የምርጫ ክልል በመውሰድ በምርጫ ጣቢያው በመገኘት የምርጫ ሂደቱን እንድትታዘቡ ለማስታወስ እንወዳለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዉ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለድምፅ መስጫና ለኦፕሬሽን ሥራዎች የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን ከማዕከል ወደ ምርጫ ክልሎች አሰራጭቶ አጠናቀቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለድምፅ መስጫና ለኦፕሬሽን ሥራዎች የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን ከማዕከል ወደ ምርጫ ክልሎች አሰራጭቶ አጠናቀቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. በሐረሪ ክልል፣ በሶማሌ ክልል እና በደ/ብ/ብ/ሕ ክልል ለሚያካሂደው ምርጫና ሕዝበ ውሣኔ፤ ለድምፅ መስጫና ለኦፕሬሽን ሥራዎች የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን ከማዕከል ወደ ምርጫ ክልሎች አሰራጭቶ አጠናቀቀ። ሥርጭቱ ዐርብ መስከረም 07 ቀን 2014 ዓ.ም. የተጀመረ ሲሆን ሐረሪ ክልል፣ ሶማሌ ክልል እና ደ/ብ/ብ/ሕ ክልል ላይ የሚሠራጩትን ቁሳቁሶች የጫኑ መኪኖች አዲስ አበባ ከሚገኘው የቦርዱ ጊዜያዊ መጋዘን መስከረም 11 ቀን 2014 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለድምፅ መስጫና ለኦፕሬሽን ሥራዎች የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን ከማዕከል ወደ ምርጫ ክልሎች አሰራጭቶ አጠናቀቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. በሐረሪ ክልል፣ በሶማሌ ክልል እና በደ/ብ/ብ/ሕ ክልል ለሚያካሂደው ምርጫና ሕዝበ ውሣኔ፤ ለድምፅ መስጫና ለኦፕሬሽን ሥራዎች የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን ከማዕከል ወደ ምርጫ ክልሎች አሰራጭቶ አጠናቀቀ። ሥርጭቱ ዐርብ መስከረም 07 ቀን 2014 ዓ.ም. የተጀመረ ሲሆን ሐረሪ ክልል፣ ሶማሌ ክልል እና ደ/ብ/ብ/ሕ ክልል ላይ የሚሠራጩትን ቁሳቁሶች የጫኑ መኪኖች አዲስ አበባ ከሚገኘው የቦርዱ ጊዜያዊ መጋዘን መስከረም 11 ቀን 2014 ዓ.ም. ወደየጫኑበት ምርጫ ክልል ተንቀሳቅሰው ጨርሰዋል። በአዲስ አበባና ቅርብ አካባቢዎች ለሐረሪ ተወላጆች ለተከፈቱት ምርጫ ጣቢያዎች የሚሠራጩትን ቁሳቁሶች ደግሞ የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች መድረስ ያለበትን የጊዜ እርዝማኔ ከግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ የሚጠናቀቅ ይሆናል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አመራሮች መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ለሚካሄደው ምርጫ ዝግጅት የመስክ ጉብኝት አደረጉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አመራሮች ከጳግሜ 2 እስከ ጳግሜ 5 ቀን 2013 ዓ.ም. ባሉት ጊዜያት መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ምርጫ የሚካሄድባቸውን አካባቢዎች ማለትም ሶማሌ ክልል፣ ሐረሪ ክልል እና ደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል የመስክ ጉብኝት እና ውይይቶችን አከናውነዋል። በቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ የተመራው ቡድን በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል መቀመጫ ከተማ ላይ የክልሉን ርዕሰ-መስተዳደር፣ የዞን አመራሮችንና በአካባቢው ላይ የሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎችን አግኝቶ የመስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ምርጫን የተመለከቱ አጠቃላይ የምክክር መድረክ አካሂዷል። ከድምጽ መስጫ ቀኑ በተጨማሪ በተመሳሳይ መስከረም 20 ለሚካሄደው ደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝበ ውሳኔ ውይይት ተደርጓል።

Share this post

ጥሪ ለፓለቲካ ፓርቲዎች እና ለግል እጩዎች

የግልም ሆነ የፓርቲ እጩዎች በመጪው መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም ለሚካሄደው የድምጽ አሰጣጥ ሂደት እና ደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝበ ውሳኔ የእጩ ወኪሎችን በየምርጫ ጣቢያው መመደብ እንደሚችሉ ይታወቃል። በመሆኑም የእጩ ወኪሎቻችሁን ዝርዝር እና አይነት እነዲሁም መስፈርቱን ማሟላታቸውን ከሚገልጽ ከሸኚ ደብዳቤ ጋር በየምርጫ ክልሉ ጽኅፈት ቤት እንድታቀርቡ እና የእጩ ወኪሎች መታወቂያ እንድትወስዱ ለማሳሰብ እንወዳለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም ድምፅ ለሚሰጥባቸው የምርጫ ክልሎች ማለትም በሃረሪ ክልል፣ በሶማሌ ክልል የተወሰኑ ምርጫ ክልሎች እና ደ/ብ/ብ/ህ ክልል ምእራብ ኦሞ ዞን የመራጮች ምዝገባን ሲያከናውን መቆየቱ እና የምዝገባው እለትም ዛሬ ጷግሜ 05 ቀን እንደሚጠናቀቅ ይታወሳል። በተለያዩ ቦታዎች ለመመዝገብ ፈልገው እድሉን ያላገኙ ዜጎችን ለማካተት ሲባል በተጨማሪነት ምዝገባው መስከረም 02 ቀን 2014 አ.ም እሁድ እንዲከናወን መወሰኑን እያሳወቅን የመራጮች ምዝገባ የመጨረሻ ቀን መስከረም 02 ቀን 2014 መሆኑን በመገንዘብ የፓለቲካ ፓርቲዎች፣ የመራጮች ትምህርት ሰጪዎች እና ሚዲያዎች ዜጎች ተጨማሪውን ቀን ተጠቅመው እንዲመዘገቡ እንዲያበረታቱ እየጠየቅን የምርጫ አስፈጻሚዎችም በተጨመረው አንድ ቀን የመራጮች ምዝገባን በምርጫ ጣቢያው ተገኝተው እንዲያከናውኑ እናሳስባለን

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ለብዙኃን መገናኛ ቀደም ሲል የተሰጠን ባጅ የአገልግሎት ጊዜ አስመልክቶ የተሰጠ ማብራሪያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛ አጠቃላይ ምርጫን መዘገብ ለሚፈልጉ ለሀገር ውስጥና ለውጭ የብዙኃን መገናኛ አካላት እና ጋዜጠኞች በተለያየ ጊዜ የፍቃድ ጥያቄያቸውን ለቦርዱ እንዲያቀርቡ ጥሪ በማድረግ መዘገብ የሚያስችላቸውን ልዩ የዘገባ ባጅ መስጠቱ ይታወቃል። ልዩ ባጅ የወሰዱ የሀገር ውስጥ የብዙኃን መገናኛ አካላት እና ጋዜጠኞች ቦርዱ በቀጣይ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ምርጫ ባልተደረገባቸው አካባቢዎችና የድጋሜ ምርጫ እንዲሁም የሕዝበ ውሣኔ የሚያካሂድባቸው አካባቢዎች አስመልክቶ የሚኖረው የምርጫ ሂደትን ለመዘገብ ቀደም ሲል ቦርዱ የሰጣቸውን ባጅ እንደሚጠቀሙ ለማሳወቅ ይወዳል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን ጋር በመተባበር መስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. በሚደረገው ምርጫ ላይ ለሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች የሚውለውን የነፃ ዐየር ሰዓት ድልድል አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሐሴ 28 ቀን 2013 ዓ.ም ከኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን ጋር በመተባበር በመጪው መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ምርጫ በሚደረግባቸው አካባቢዎች ላይ ለሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች የሚውለውን የነፃ ዐየር ሰዓት ድልድል አካሄደ። የዐየር ሰዓት ድልድሉ መመሪያውን መሠረት አድርጎ፤ በሶማሌ ክልል፣ በሐረሪ ክልል እና በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል ለሚወዳደሩ 22 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 106 የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች የቀረበ ሲሆን፤ ይህውም በሦስት ሬዲዮ ጣቢያዎች፣ በአራት ቴሌቪዥንና በሁለት ጋዜጦች ላይ ተከናውኗል።

Share this post

የሴት የፖለቲካ ፓርቲ አባላት የጋራ ምክር ቤት ምሥረታ ተካሄደ

ዛሬ ነሐሴ 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ሴት የፖለቲካ ፓርቲ አባላት የጋራ ምክር ቤት ምሥረታ ጉባዔ ተካሄደ። የቦርዱ አመራር አባላት የሆኑት ብዙወርቅ ከተተ፤ አበራ ደገፋ (ዶ/ር)፣ ፍቅሬ ገ/ሕይወት፣ ውብሸት አየለ እንዲሁም የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲ አባል የሆኑ ሴቶች የተሣተፉበትን ይህንን ጉባዔ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ውብሸት አየለ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ሴቶች በፓለቲካ ያላቸው ተሣትፎ እጅግ አነስተኛ እንደሆነ ገልጸው ቦርዱም ይህን እንዲሻሻል ይርዳ ዘንድ የተለያዩ ሥራዎችን ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመሥራት ቢሞክርም ከሚፈለገው ለውጥ አንጻር ግን ብዙ የሚቀሩ ሥራዎች እንዳሉ ገልጸዋል። የጋራ ምክር ቤቱን የመመሥረት ውጥን ሁለት ዓመታት እንዳሳለፈና ትልቅ ፋይዳም እንደሚኖረው ተናግረዋል።

Share this post