Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የወጣቶች የክርክር መድረክን አዘጋጀ

የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኮሚኒቲ ሰስተነብል ዴቬሎፕመንት ኤይድ ከተባለ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር በ 3 የተለያዩ ከተሞች ማለትም ወላይታ ሶዶ፥ ሆሳዕና እና ወልቂጤ የክርክር መድረክ አካሂዷል። ይህ የክርክር መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፥ በሆሳዕና ከተማ ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም በወልቂጤ ከተማ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተካሄደ ሲሆን የሕግ ትምህርት ቤት ተማሪዎች እና የዩኒቨርሲቲዎቹ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። ክርክሩም በዋናነት በምርጫ ፥ዲሞክራሲና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ሲሆን ተማሪዎች በንድፈ-ኃሳብ ደረጃ የተማሯቸውን ፅንሰ-ሀሳቦች ተግባራዊ እንዲያደርጉ እድል ያመቻቸ መድረክ መሆኑ ተጠቅሷል።

Share this post

ቦርዱ የ6ኛውን ሀገር አቀፍ ቀሪና የድጋሚ ምርጫ ውጤት ይፋ አድርጓል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቤንሻንጉል-ጉሙዝ፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ያካሄደውን የ6ኛው ዙር ሀገር አቀፍ ቀሪና የድጋሚ ምርጫ ውጤት ሰኔ 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል።

የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ በተጠቀሱት አራቱ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ 29 ምርጫ ክልሎች ስር በሚገኙ በ1218 ምርጫ ጣቢያዎች መካሄዱ የታወቀ ሲሆን ውጤት ይፋ በማድረጊያ መርኃ-ግብሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች (ተወካዮች)፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያቀረቡአቸው ዕጩዎች፣ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኃላፊዎችና ተወካዮች፣ የሚዲያ አካላት፣ የፌዴራልና የክልል የጸጥታ አካላት እና ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች ታዳሚ ነበሩ።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሴንተር ፎር ኢምፓዎርመንት ኢትዯጵያ አሶሲዬሽን ከተባለ የሲቪል ማህበር ድርጅት ጋር በመተባበር የክርክር መድረክ አካሄደ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት የሥራ ክፍል የተለያዩ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶችን በማቀናጀት እና የተመረጡ ውጤታማ ዘዴዎችን በመጠቀም በምርጫ ዲሞክራሲያዊ ሂደት ፥ የዜጎች ተሳትፎና ተያያዥ ርዕሰ-ጉዳዮች ዙሪያ ት/ት እየሰጠ ይገኛል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሴንተር ፎር ኢምፓዎርመንት ኢትዯጵያ አሶሲዬሽን ከተባለ የሲቪል ማህበር ድርጅት ጋር በመተባበር ከግንቦት 24/2016 ጀምሮ በሦስት ዙር የተከፋፈለ የክርክር መድረክ በወላይታ ሶዶ፥ ወራቤ እና ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ ተማሪዎችን በማሳተፍ አካሂዷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ‘ውመን ኢን ማይስ ኢትዮጵያ’ ከተባለ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር በዲሞክራሲያዊ ምርጫ ሂደት እና የሴቶች ተሳትፎ ላይ ያተኮረ የክርክር መድረክ በወላይታ ዞን የተለያዩ ከተሞች አካሄደ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕግ ከተሰጡት ኃላፊነቶች መካከል አንዱ ዜጎች በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲደርጉ የስነ- ዜጋና መራጮች ትምህርትን ማዳረስ ነው። በመሆኑም ቦርዱ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም የመራጮች መረጃ እና ትምህርትን ወደ ማህበረሰቡ ለማድረስ ከተለያዩ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በጋራ እየሠራ ይገኛል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች የሚያስፈጽመውን የ6ኛው ዙር ቀሪና እና የድጋሚ ምርጫን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. የ6ኛው ዙር ቀሪና እና የድጋሚ ምርጫ ድምፅ የመስጠት ሂደትን እንደሚያስፈጽም ይታወቃል። በዚህም መሠረት በዕለቱ የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ ድምፃቸውን መስጠት እንዲችሉ፤ እንዲሁም የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከናወን ለማስቻል፤ ቦርዱ የሚከተሉትን ተግባራት ተፈጻሚ እንዲሆኑ “የምርጫ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የሥነ‐ምግባር ዐዋጅ 1162/ 2011 አንቀጽ 161” ላይ በተደነገገው የመተባበር ግዴታ መሠረት ለመንግሥታዊና መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት ከታች የተዘረዘሩትን ተግባራት ያሳውቃል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. የሚያደርገውን የ6 ኛው ዙር ቀሪና የድጋሚ ምርጫን ለመዘገብ ከቦርዱ እውቅና ላገኙ የመገናኛ ብዙኃን ሰኔ 12 ቀን 2016 ዓ.ም. ሥልጠና ሠጠ፡፡

ስልጠናው የመገናኛ ብዙኃን እና የጋዜጠኞች የምርጫ አዘጋገብ ስነ ምግባርን ላይ አትኩሮት አድርጎ የምርጫ ዑደትና የምርጫ ሕግ ማዕቀፍን፤ ምርጫውን የተመለከቱ አጠቃላይ መረጃዎችን፤ አካታች የምርጫ ዘገባ ባህሪያትን እና የተዛቡ፤አሳሳች፤አደናጋሪና በአጋጣሚ ወይም ሆን ተብለው የሚፈጠሩ የመረጃ መዛባቶችን እና የመረጃዎችን ትክክለኛነት ለመፈተሽ በሚያስችሉ የዲጂታል እውቀቶች እና አጠቃቀሞች ዙሪያ ያተኮረ ነበር፡፡

Share this post