Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ). ሰኔ 25 እና 26 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ በተመለከተ በቀረቡለት አቤቱታዎች ላይ ተከታዮቹን ውሣኔዎች አስተላልፏል

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ አባል የሆኑት እነአቶ ዘመኑ ሞላ (ስድስት ሰዎች) ነሐሴ 16 ቀን 2014 ዓ.ም. ጽፈው ባቀረቡት አቤቱታ ፓርቲው ሰኔ 25 እና 26 ቀን 2014 ዓ.ም. ባከናወነው 1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ የተለያዩ የደንብ ጥሠቶች ተፈጽመዋል በማለት ለቦርዱ ሰኔ 21 እና 29 እንዲሁም ሐምሌ 5 ቀን 2014 ዓ.ም. ያቀረቡትን አቤቱታ ለማጠናከር ይረዳል ያሉትን ተጨማሪ ማስረጃዎችን አቅርበዋል። በሌላ በኩል እነአቶ ደሳለኝ በዛብህ (ሁለት ሰዎች) እንዲሁ ሰኔ 29 ቀን 2014 ዓ.ም. በተጻፈ ደብዳቤ ተመሳሳይ አየቱታ አቅርበዋል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚያካሄደው ሕዝበ ውሳኔ የ541 ሚሊዮን ብር የበጀት ጥያቄ አቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ውስጥ ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ ማስፈጸሚያ የሚያስፈልገውን የአምስት መቶ አርባ አንድ ሚልዮን ሁለት መቶ ሰባ ሺህ አንድ መቶ አራት ብር ከሰማንያ ሁለት ሳንቲም (የ541,270,104.82) በጀት ያቀረበው ለኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው።

ቦርዱ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር የሚገኙ ስድስት ዞኖች ማለትም የጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ጌዲዮ፣ ኮንሶና፣ ደቡብ ኦሞ ዞኖች እንዲሁም አምስት ልዩ ወረዳዎችን እነዚሁም የቡርጂ፣ አማሮ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ ልዩ ልዩ ወረዳዎች ላይ ሕዝበ ውሳኔ እንደሚያካሄድ ይታወቃል።

Share this post

የብልፅግና ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤን አስመልክቶ በቦርዱ የተሰጠው ውሳኔ ማጠቃለያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ብልጽግና ፓርቲ ከመጋቢት 2 እስከ 4 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ያደረገውን 1ኛ ጠቅላላ ጉባዔ አስመልክቶ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ለፓርቲው አሳውቋል።

በዚህም መሠረት የውሳኔው አንኳር ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦

በፓርቲው በጉባዔው የተመረጡ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ዝርዝር የቦርዱ ታዛቢዎች በወቅቱ የምርጫው ውጤት ሲገለፅ መዝግበው ካቀረቡት ዝርዝር ጋር ልዩነት መኖሩን አረጋግጦ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላቱ ቦርዱ ምርጫውን ሲታዘቡ መዝግቦ የያዛቸው መሆናቸውን በመጨረሻ የወሰነ ሲሆን ስም ዝርዝራቸውንም ከውሳኔው ጋር አያይዞ ልኳል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአካባቢ ምርጫ የሕግ ማዕቀፍ እና አፈጻጸምን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአካባቢ ምርጫ የሕግ ማዕቀፍ እና አፈጻጸምን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት ያካሄደው ነሐሴ 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ነው፡፡ የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳን ጨምሮ የቦርድ አመራር አባላትና የጽ/ቤት ኃላፊ በተገኙበት ውይይት፤ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ተወካይ ተሳትፈዋል፡፡

Share this post

ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 1133/2011 ዓ.ም. እና በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 ዓ.ም. መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመመዝገብ ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡

በዚህም መሠረት በዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 66 ንዑስ አንቀጽ አንድ ላይ ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ በኢትዮጵያ ውስጥ በፖለቲካ ፓርቲነት ለመንቀሳቀስ የሚችለው በሕጉ መሠረት በቦርዱ ተመዝግቦ የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሲያገኝ ብቻ እንደሆነ ተደንግጓል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለክልል ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ሠራተኞች የሕግ ማዕቀፍ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሕግ ማዕቀፍ ላይ በማተኮር ለቦርዱ የክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችና ሠራተኞች ሥልጠና የሰጠው ነሐሴ 10 እና 11 ቀን 2014 ዓ.ም ነው።

ሥልጠናው በቦርዱ አመራር አባል የሆኑት ፍቅሬ ገ/ሕይወት ንግግር ተከፍቷል። አመራሩ በንግግራቸው የቦርዱ የክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችና ሠራተኞች እንዲሁም የምርጫ አስፈጻሚዎች በ6ተኛው ሀገራዊ ምርጫ የነበራቸውን አስተዋፅዖ በማንሳት ምሥጋና አቅርበዋል።

አያይዘውም ቦርዱ እንደ አዲስ የተቋቋመ በመሆኑ በጊዜው በርካታ እቅዶች ቢኖሩም ከጊዜና ከሁኔታዎች አንጻር የታቀደውን ሁሉ በሚፈለገው መጠን መፈፀም እንዳልተቻለ የጠቆሙ ሲሆን፣ አሁን ግን እነዚህን ጉዳዮች ለመተግበር አመቺ ሁኔታ ስለተፈጠረ በተለይ በቀጣይ ለሚደረገው ትልቅ ዐቅም ለሚጠይቀው የአካባቢ ምርጫ ይህ ሥልጠና የሚኖረውን አስተዋፅዖ አብራርተዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአካባቢ ምርጫ የሕግ ማዕቀፍ እና አፈጻጸምን የተመለከተ ያስጠናው ጥናት ላይ ባለድርሻ አካላትን አወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሐሴ 9 ቀን 2014 ዓ.ም. የአካባቢ ምርጫ የሕግ ማዕቀፍ እና አፈጻጸምን የተመለከተ ያስጠናው ጥናት ላይ ባለድርሻ አካላትን አወያየ። የውይይቱ ዋና ዐላማ በኢትዮጵያ ለ5ኛው ጊዜ የሚካሄደውን የአካባቢ ምርጫ ለማከናወን በሚደረገው ዝግጅት ላይ የአካባቢ ምርጫን አጠቃላይ ባህሪና አሠራር አስመልክቶ ምርጫ ቦርዱ ባስጠናው ጥናት ላይ ጥናቱ የተከናወነባቸውን ሳይንሳዊ ዘዴዎች፣ በጥናቱ የተገኙ ልምዶችን ፣ ተግዳሮቶችን፣ እንዲሁም ምክረ ሃሳቦችን ጥናቱን ባካሄዱት በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የፈደራሊዝም እና አስተዳድር ጥናት/ ትምህርት ክፍል (Centre for Federalism and Governance Studies Addis Ababa University) በሚሠሩ ከፍተኛ የዘርፉ ተመራማሪዎች በማቅረብ አፈጻጸሙን አስመልክቶ ባለድርሻ አካላትን በማወያየት ሃሳብ ለመሰብሰብ ያለመ ነው።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አ.ብ.ን በድጋሜ የሚያካሂደው ጠቅላላ ጉባዔን አስመልክቶ የቀረቡ ሪፖርቶች ላይ ውሣኔ አሣለፈ

የተወሠነበት ቀን ሐምሌ 25 ቀን 2014 ዓ.ም.

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) መጋቢት 11 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ እና መጋቢት ዘጠኝ እና ዐሥር 2014 ዓ.ም. የተካሄደውን የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባን አስመልክቶ ያቀረበውን ሪፖርት ተከትሎ ቦርዱ ሚያዝያ 13 ቀን 2014 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ ፓርቲው ከሪፖርቱ ጋር አያይዞ ያቀረባቸውን ሠነዶች ከሕጉና ከመተዳደሪያ ደንቡ አንጻር መርምሮ ያሣለፈው ውሣኔ ሚያዝያ 18 ቀን 2014 ዓ.ም. በቁጥር አ1162/11/586 በተጻፈ ደብዳቤ ለፓርቲው ገልጿል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ የፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባና ሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በእነ ዶክተር አዲሱ መኮንን አማካኝነት ገቢ በሆነ ደብዳቤ «አገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ)» በሚል ስያሜ በክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲነት ለመመዝገብ የዕውቅና ጥያቄ ቀርቦለት የነበረ ሲሆን፤ ቦርዱም የቀረቡትን ሠነዶች በሕጉ መሠረት በመመርመር ያልተሟሉ ሠነዶች እንዲሟሉና መስተካከል ያለባቸውም እንዲሁ እንዲስተካከሉ በማድረግ፤ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 1133/2011 እና በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 በተሰጠው የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመመዝገብ ኃላፊነት መሠረት «አገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (ፍትህ)»ን የክልል የፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባና ሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሐምሌ 19 ቀን 2014 ዓ.ም. ሰጥቶቷል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሐምሌ 25 ቀን 2014 ዓ.ም.

Share this post