Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቀድሞ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) ንብረት እንዲያጣሩ ሁለት ኦዲተሮችን ሾመ

ሰኔ 6 ቀን 2012 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሰረት ጥር 20 ቀን 2012 ዓ.ም ኢሕአዴግ እንዲፈርስ እንዲሁም የቀድሞ ሶስቱ የግንባሩ አባላት ወራሽ የሆነው ብልጽግና ፓርቲ እና በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሐት) በስድስት ወር ውስጥ የንብረት ክፍፍል ተጠናቆ እንዲያቀርቡ ክፍፍሉም የሶስት ፓርቲዎች ወራሽ የሆነው ብልፅግና የሃብቱን ሶስት አራተኛ (3/4) በራሱ ህጋዊ እውቅና ያለው ህወሃት አንድ አራተኛ ( ¼) እንዲወስዱ መወሰኑ ይታወሳል፡፡ በውሳኔውም ፓርቲዎቹ የጋራ ንብረት አጣሪ ሾመው የባለመብቶችን (creditors) መብት እንዲጠበቅ እንዲሁም በተገለጸው ቀመር መሰረትም የንብረት ክፍፍሉ እንዲፈጸም ወስኖ አሳውቆ ነበር፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለህገመንግስት አጣሪ ጉባኤ ያቀረበው ጥናት

ግንቦት 13 ቀን 2012 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 13 ቀን 2012 ዓ.ም ለህገመንግስት አጣሪ ጉባኤ ያቀረበው ጥናት ከስር ማግኘት ይቻላል፡፡

ጥናቱ ቦርዱ እስካሁን የሰራቸውን ስራዎች፣ አሁን እየሰራቸው ያሉ ስራዎች እና ለወደፊቱ ለማድረግ የሚችላቸውን አማራጮች ያቀረበበት ሲሆን እነዚህ ጥናቱ ላይ የተጠቀሱ ሁኔታዎች ወደፊት በሚያጋጥሙ አዳዲስ ሁኔታዎች እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት በሚገኙ ግብአቶች ሊቀየሩ የሚችሉ ናቸው፡፡

ከጥናቱ ጋር ተያይዞም ከድሮው የጊዜ ሰሌዳ አንጻር አዳዲስ ጊዜ ሰሌዳ አማራጭችም የቀረቡ ሲሆን ይህም ለጉባኤው ውሳኔ እንዲሁም በአጠቃላይ የምርጫ ኦፕሬሽንን ለመረዳት እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሀያ ሰባት (27) ፓርቲዎችን ሰረዘ

ሰኔ 3 ቀን 2012 ዓ.ም. 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እስከ መጋቢት 3 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ በቀድሞ ህግ ሰርተፍኬት የነበራቸው እና በቀድሞው ህግ ምዝገባ ጀምረው ለነበሩ መቶ ስድስት (106) ፓርቲዎች በአዲሱ ህግ ላይ የተቀመጡ መስፈርቶችን እንዲያሟሉ በደብዳቤ ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ ከቦርዱ ደብዳቤ ከደረሳቸው መቶ ስድስት (106) የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ሰባ (76) የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰነዶችን ያቀረቡ ሲሆን በሕጉ መሠረት ተሟልቶ የቀረበ ስለመሆኑ እየተመረመረ ይገኛል፡፡ 

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 27 ፓርቲዎችን ሰረዘ

ግንቦት 7 ቀን 2012 ዓ.ም 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እስከ መጋቢት 3 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ በቀድሞ ህግ ሰርተፍኬት የነበራቸው እና በቀድሞው ህግ ምዝገባ ጀምረው ለነበሩ 106 ፓርቲዎች በአዲሱ ህግ ላይ የተቀመጡ መስፈርቶችን እንዲያሟሉ በደብዳቤ ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ ከቦርዱ ደብዳቤ ከደረሳቸው 106 የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል 76 የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰነዶችን ያቀረቡ ሲሆን በሕጉ መሠረት ተሟልቶ የቀረበ ስለመሆኑ እየተመረመረ ይገኛል፡፡

ጥያቄ - የቦርዱ ስራ ከዚህ በኃላ ምን ይሆናል?

መልስ - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአሁኑ ወቅት አብዛኛው ሰራተኞቹ ከቤት ሆነው የቀረው ደግሞ በፈረቃ ስራውን በማከናውን ላይ ሲሆን መሰብሰብ የማያስፈልጋቸው ስራዎቹን ማህበራዊ መራራቅን ተግባራዊ በማድረግ እየሰራ ይገኛል፡፡ የቦርዱን የምርጫ አፈጻጸም ዝግጁነት የሚጨምሩ፣ሁኔታው ተቀይሮ ተቋሙ ወደ መደበኛ ተግባሩ ሲመለስ በተገቢው ሁኔታ ምርጫን ለማስፈጸም የሚያሥችል ሁኔታን የሚፈጥሩ ተግባራትን እያከናወነ ይቆያል፡፡ በዚህም መሰረት የፓለቲካ ፓርቲዎቸን ዲጂታል ኮምኒኬሽን መረጃ እየሰበሰበ ይገኛል፡፡ ከፓርቲዎች ጋር የሚኖረው ግንኙነትም በተቻለ መጠን በዲጂታል መንገድ ለማድረግ ጥረት ያደርጋል፡፡ 

ጥያቄ - ኮቪድ19 እና ምርጫው ላይ የሚኖረውን ተጽእኖ አስመልክቶ የፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር አልተደረገም ነበር?

መልስ - ቦርዱ የኮቪድ19 በምርጫ ላይ የሚኖረውን ተጽእኖ አስመልክቶ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር አድርጓል፡፡ ያደረገው ምክክር በሁለት ዙር ሲሆን በእለቱም ፓለቲካ ፓርቲዎች የተለያዩ አስተያየቶችን ሰጥተዋል፡፡ የሰጧቸው አስተያየቶችም ችግሩን አለም አቀፍነት በተለይ ደሞ እንደኢትዮጵያ ላለ አገር ሊያስክተል የሚችለውን ቀውስ እና በምርጫ ስራ ላይ የሚያመጣውን ተጽእኖ እንደሚረዱ ገልጸዋል፤ ምርጫ ቦርዱ ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በመመካከር እንዲሰራም ጠይቀዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ቦርዱ ምክክሩን ማድረጉን አድንቀው መንግስት ያስቀመጠው የ14 ቀን ክልከላ ታይቶ ቢወሰን የሚል አማራጭም አቅርበዋል፡፡ ውይይቱ በመግባባት የተጠናቀቀ ሲሆን የፓርቲ አመራሮች ይህንን እድል የአገራችንን ፓለቲካ ለማስተካከልም ሆነ በቂ ዝግጅት ለማድረግ መጠቀም እንደሚገባ፣ ይህ ውሳኔ በቦርዱ መወሰን እንዳለበት እና ፓርቲዎችን ማማከር ጥሩ ቢሆንም ውሳኔው ከፓርቲዎች በላይ መሆኑን እና በአገር የመጣ ከአቅም በላ

ጥያቄ - ቦርዱ ውሳኔውን ለተወካዮች ምክር ቤት ያሳወቀው ለምንድነው?

መልስ - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርዱ ተጠሪነቱ ለተወካዮች ምክር ቤት ነው፡፡ የአፈጻጸም ሪፓርቶችን የሚያቀርበውም ለምክር ቤቱ ነው በመሆኑም ውሳኔውን ለተወካዮች ምክር ቤት ከማሳወቅ ውጪ ሌላ አማራጭ የለውም፡፡ ቦርዱ በተሰጠው ሃላፊነት መሰረት ችግሩን ለተወካዮች ምክር ቤት ከማቅረብ እና በጥናት ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ከማድረግ ውጨ ከስልጣኑ ውጪ የሰራው ወይም ስልጣኑ ኖሮት ሳይወጣ የቀረው ሃላፊነት የለም፡፡

ጥያቄ - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው መግለጫ ምርጫውን አራዝሟል? የመግለጫው ዋና ሃሳብ ምንድነው?

መልስ - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 24 ቀን 2012 ዓ.ም መግለጫ አውጥቷል፡፡ በመግለጫው ዋና አላማ ምርጫውን ቀድሞ ባቀደው ቀን ማለትም ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ማከናወን እንደማይችል ማሳወቅ ሲሆን፣ እዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ጥናት አካሂዷል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተጠሪነቱ ለተወካዮች ምክር ቤት ስለሆነ ውሳኔውንም ለተወካዮች ምክር ቤት አሳውቋል፡፡ ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ምርጫውን ማከናወን ካለመቻሉ በስተቀር የተራዘመ ቀን ቆርጦ አላቀረበም፡፡ ቦርዱ ማድረግ የሚችለው አለመቻሉን ብቻ ገልጾ ሪፓርት ለሚያደርግለት ለተወካዮች ምክር ቤት ማሳወቅ ብቻ ነው፡፡ 
በመግለጫው ተገለጹት የቦርዱ ዋና ዋና ውሳኔዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ 
• በኮቪድ19 የተነሳ ቦርዱ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ምርጫውን ማካሄድ የማይቻለው መሆኑን በመረዳት ያወጣውን የጊዜ ሰሌዳ በመሰረዝ በሰሌዳው መሰረት መከናወን ያለባቸው ተግባራት ለጊዜው እንዲቆሙ ፤