• Birtukan_Mideksa_chiarperson
    ብርቱካን ሚደቅሳ የቦርድ ሰብሳቢ
    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሊቀ መንበር ብርቱካን ሚደቅሳ፥ በ1966 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ተወለዱ። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ፣ የፌዴራል ፍርድ ቤት ዳኛ ሆነው ሠርተዋል፡፡
  • wubshetnew
    ውብሸት አየለ የቦርድ ምክትል ሰብሳቢ
    አቶ ውብሸት አየለ፣ በ1947 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ የተወለዱ ሲሆን፣ በ1980 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በህግ ትምህርት የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል
  • jghjhgj
    አበራ ደገፋ (ዶ/ር) የቦርድ አባል
    ዶ/ር አበራ ደገፋ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተባባሪ ፕሮፌሰር ናቸው፡፡ በህግ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን የሠሩት በዚሁ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን፣ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በሶሻል ወርክ እና ሶሻል ዴቨሎፕመንት ከዚሁ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል፡፡
  • iliul
    ብዙወርቅ ከተተ የቦርድ አባል
    በ1952 ዓ.ም. የተወለዱት ብዙወርቅ ከተተ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በግሪክ፣ የከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኩባ ሐቫና ዩኒቨርሲቲ የውጪ ቋንቋዎች ትምህርት ክፍል በሥነ ቋንቋ የሁለተኛ ደረጃ ዲግሪ አግኝተዋል፡፡
  • ፍቅሬ ገ/ሕይወት

    የቦርድ አባል


    አቶ ፍቅሬ ገ/ሕይወት ከአምስቱ የቦርድ አመራር አንዱ ናቸው። አቶ ፍቅሬ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በሕግና በታሪክ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያገኙ ሲሆኑ፤ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በልማት ጥናቶችና በፕሮጀክት አስተዳደር አግኝተዋል።