በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በመሥክ አሠልጣኝነት ለተሣተፉ ባለሞያዎች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በመሥክ አሠልጣኝነት ለተሣተፉ ባለሞያዎች ለነበራቸው የላቀ ተሣትፎ እያመሰገነ፤ በምርጫው ላይ በአሠልጣኝነት የነበራቸውን ተሣትፎ የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት በቀላሉ ለመውሰድ የሚያስችል የምስክር ወረቀት መውሰጃ ፖርታል አዘጋጅቶ አቅርቧል።

የምስክር ወረቀቱ የሚመለከታቸው ባለሞያዎች ከሥር የሚገኘውን ሊንክ በመጫንና የምስክር ወረቀት ፖርታሉ ላይ የሚጠየቁትን የማንነት ማረጋገጫ መረጃ በማስገባት የምስክር ወረቀታቸውን መውሰድ የሚችሉ መሆኑን ቦርዱ ይገልጻል።

እዚህ ላይ ይጫኑ

ማስታወቂያ
ሰኔ 28, 2014