የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛውን ዙር ጠቅላላ ምርጫ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ባላካሄደባቸው እና ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው ምርጫ ክልሎች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝበ ውሣኔ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ያከናወነ መሆኑ ይታወቃል፡፡

በዚሁ መሠረት ቦርዱ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ምርጫ አስመልክቶ አቤቱታ ያላችሁ ከሆነ ከመስከረም 22 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ እስከ መስከረም 26 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ቦርዱ ባዘጋጀው የአቤቱታ ማቅረቢያ ቅፅ በመሙላት በስካይላይት ሆቴል በሚገኘው የቦርዱ ዴስክ እንድታቀርቡ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

ማስታወቂያ
መስከረም 22 ቀን 2014 ዓ.ም