እንደሚታወቀው የ6ተኛው አገራዊ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ እየተከናወነ ይገኛል።

1, የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ዘግይቶ የተጀመረባቸው ቦታዎች በመኖራቸው

2, የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ላይ የቁሳቁስ ስርጭት የዘገየባቸው ቦታዎች በመኖራቸው

3, ድምፅ ለመስጠት ረጅም ሰልፉች ላይ ያሉ ዜጎች በመኖራቸው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት እስከ ምሽቱ 3 ሰአት ድረስ መራዘሙን ቦርዱ ያሳውቃል። በዚህም መሰረት የምርጫ አስፈፃሚዎች እስከ 3 ሰአት ድረስ የሚመጣ ማንኛውንም መራጭ እንዲያስተናግዱ ጥሪ እናስተላልፋለን። ነገር ግን የመራጮች መዝገባቸው ላይ ያሉ ዜጎች መርጠው ያጠናቀቁባቸው እና ለመምረጥ የተሰለፉ ዜጎች በተጠናቀቁበት ቦታዎች የምርጫ ጣቢያ መዝጋት እና የቆጠራ ስራ መጀመር ይችላሉ።

በድምፅ አሰጣት ሂደት ወቅት ችግር ያጋጠማቸው ዜጎች 778 ነጻ የስልክ መስመር በመደወል ማሳወቅ ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ማስታወቂያ
ሰኔ 14 ቀን 2013 አ.ም