የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አገራዊ ምርጫ ኦፕሬሽን እያደረገ ያለውን ዝግጅት ለሚዲያ አካላት ማስጎብኘት ይፈልጋል። በመሆኑም በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የተመዘገባችሁ ሚዲያዎች በሙሉ እንድትጎበኙ ተጋብዛችኃል።

የምርጫ ቁሳቁሶቹ በከፍተኛ ጥበቃ ስር የሚገኙ በመሆናቸው አንድ ሪፓርተር እና አንድ የካሜራ ባለሞያ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር እንዲሁም የሚድያውን ስም ወደ medianebe@gmail.com የኢሜል አድራሻ እስከ ነገ እረቡ ምሽት መስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም 12 ሰአት ድረስ እንድትልኩልን እንጠይቃለን። በጉብኝቱ የሚሳተፉት ስማቸው የተላለፉ ባለሞያዎች ብቻ ይሆናል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የጥሪ ማስታወቂያ
መስከረም 19 ቀን 2013 ዓ.ም