ፍቅሬ ገ/ሕይወት


አቶ ፍቅሬ ገ/ሕይወት ከአምስቱ የቦርድ አመራር አንዱ ናቸው። አቶ ፍቅሬ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በሕግና በታሪክ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያገኙ ሲሆኑ፤ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በልማት ጥናቶችና በፕሮጀክት አስተዳደር አግኝተዋል። ከ2000 ዓ.ም አንሥቶ በአዲስ አበባና በተለያየ ዩኒቨርስቲዎች ከማስተማራቸው ባሻገር በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የአስተዳደር ዕርከኖች ላይ አገልግለዋል። የተለያዩ የምርምር ስራዎችን የሠሩት አቶ ፍቅሬ ለመንግሥታዊና መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት አጫጭር ሥልጠናዎችን መስጠት ችለዋል። ከዚህ በተጨማሪም የዜና-ልሳን (Journal of the Academy of Ethiopian Languages and Cultures) አስተዳዳሪ አርታኢ እንዲሁም SINET መጽሔት ዋና አዘጋጅ በመሆን አገልግለዋል።