የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 1133/2011 እና በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመመዝገብ ኃላፊነት ተሰጥቶታል።

በዚሁ መሠረት በእነአቶ ዩሱፍ ሁሴን “የሱማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ (ሱ.ፌ.ፓ)” በሚል ስያሜ የክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ያቀረቡ በመሆኑ በዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 68 ንዑስ አንቀጽ ሁለት እና ሦስት መሠረት በፓርቲው ስም፣ ዐርማ ወይም ሌሎች ጉዳዮች ተቃውሞ ያለው ሰው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከዛሬ ኅዳር 8 ቀን 2015 ዓ. ም. ጀምሮ በ14 ቀናት ውስጥ ተቃውሞውን የቦርዱ ዋናው መሥሪያ ቤት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. 207 እንዲያቀርብ ቦርዱ ያሳስባል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ማስታወቂያ
ኅዳር 08 ቀን 2015 ዓ.ም.