Skip to main content

በድምጽ መስጫ ወቅት ስለሚተገበሩ መመሪያዎች በጥቂቱ

በድምጽ መስጫ ቦታ ወይም ከመግቢያው ስፍራ በሚሆኑበት ጊዜ የሚከተሉት ህጎች ሊተገብሩ ይገባል

ለፖለቲካ ፓርቲዎች

  • በምርጫ ቅጥር ግቢ ውስጥ ወይም ከመግቢያቸው ስፍራ መራጮቹን የሚያደናቅፍ ወይም ተጽዕኖ የሚያሳድር ማንኛውንም አደናቃፊ ነገር ማድረግ አይፈቀድም
  • በድምጽ መስጫ ወቅት መራጮች ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ማናቸውም ተጽእኖዎችን ማድረግ የተከለከለ ነው
  • በድምጽ መስጫ ወቅት የምርጫ ዘመቻ እንቅስቃሴዎችን ማድረግ እንዲሁም የቅስቀሳ ቁሳቁስ ማሰራጨት እና የፓርቲዎችን ምልክት የሚያሳዩ አልባሳት መጠቀም የተከለከለ ነው
  • ከምርጫው ወይም ከህዝበ ውሳኔ ጋር በተያያዘ እለቱ ቀን ሰልፎችን አይጥሩ
  • መራጮች ማንን እና እንዴት እንደመረጡ የሚያመለክቱ የማህበራዊ ድህረ-ገጽ ዘመቻዎችን ማከናወን አይፈቀድም
  • ወደ ድምጽ መስጫ ቦታ ለመድረስ እርዳታ ለመስጠት ሰዎችን ማነጋገር ወይም የምርጫ ቀን መሆኑን ለማስታወስ ይችላሉ ፡፡ እንዴት እንደሚመርጡ ተጽዕኖ ማድረግ የለብዎትም፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሰኔ 08 ቀን 2013 ዓ.ም

Share this post