Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአውሮፓ ኅብረትና የጀርመን መንግሥት በጋራ ያበረከቱለትን 22 መኪኖች ተረከበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም. የአውሮፓ ሕብረትና የጀርመን መንግሥት በጋራ ያበረከቱለትን 22 መኪኖች ተረከበ። የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ በተገኙበት የተፈጸመው ርክክብ 12 ሃርድ ቶፕ እና 10 ፒክ አፕ መኪኖችን ያካተተ ነው። ዋና ሰብሳቢዋ ቦርዱ የሎጀስቲክ እንቅስቃሴ ላይ ያለበትን ውስንነት ገልጸው ለተደረገው ድጋፍ ያላቸውን ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል። ቦርዱ በመንግሥትም ሆነ በአውሮፓ ሕብረት የሚደረጉለት ድጋፎች አስፈላጊነት ገልጸው፤ ለዛም ቦርዱ አመስጋኝ ነው ብለዋል።

Share this post