Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ከሐምሌ 29 እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2016 ዓ.ም. በጋና አክራ በአፍሪካ ሴት የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢዎች መካከል በተካሄደው በስትራቴጂካዊ የልምድ ልውውጥ መድረክ ላይ ተሣተፉ

የመድረኩ ዐላማም በምርጫ አስተዳደር አመራርነት ባሉ ሴት የቦርድ ሰብሳቢዎች መካከል የአቻ ላቻ ትብብርና ትሥሥር መፍጠር፤ እንዲሁም በአፍሪካ ደረጃ የሚያጋጥሙ ውስብስብ የምርጫ ዐውዶችን መልስ በመስጠት ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማንበር አስቻይ ሁኔታዎችን እንዴት መፍጠር ይቻላል የሚሉት ይገኙበታል። በአፍርካ ደረጃ ዘጠኝ ሴት የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢዎች ሲኖሩ፤ ኢትዮጵያ ከነዚኽ ሀገራት ውስጥ ተጠቃሽ ናት።

Share this post