Skip to main content

የእጩዎች የመጨረሻ ዙር የማጣራት ሂደት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛውን ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. እንደሚያከናውን ይታወቃል ነገር ግን ስማችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘረው ግለሰቦች በ 2013 ዓ.ም በ6ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ወቅት እጩ የነበራችሁ ሲሆን አሁን በምናደርገው ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ እንድትሳተፉ በቦርዱ የመረጃ ቋት ውስጥ ባላችሁ ስልክ ቁጥር በመደወል ለማግኘት የተደረገው ጥረት ስልካችሁ ሊሰራ ባለመቻሉ ምክንያት ሊሳካ አልቻለም። ይሁን እንጂ ቦርዱ በምርጫ አዋጁ 1162/2011 አንቀጽ 39 (2) መሰረት የእጩዎችን የመወዳደር መብት ለመጠበቅ የመጨረሻ ማጣራት እያከናወነ ይገኛል፡፡

በዚህ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘረው ግለሰቦች አስከ ግንቦት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. እስከ ጠዋቱ አራት ሰዓት ድረስ በስልክ ቁጥር 0995003794 በመደወል እንድታሳውቁ ቦርዱ ጥሪ ያቀርባል፡፡

የስም ዝርዝር ለማየት እዚህ ላይ ይጫኑ

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post