Skip to main content

እጩ ከነበራችሁበት ፓርቲ መልቀቃችሁን ስለማሳወቅ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛውን ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. እንደሚያከናውን ይታወቃል፡፡ ለዚህም ይረዳ ዘንድ የዕጩ ምዝገባ ከሚያዝያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን ስማችሁ ከዚህ በታች የተገለጹት የፓርቲያችሁ አባላት በዚህ ምርጫ እንደማይሳተፉ እና በሌላ እጩ መተካታቸውን አሳውቃችሁናል፡፡ ይሁን እንጂ ቦርዱ በምርጫ አዋጁ 1162/2011 አንቀጽ 39 (2) መሰረት የእጩዎችን የመወዳደር መብት ለመጠበቅ የመጨረሻ ማጣራት እያከናወነ ይገኛል፡፡

በመሆኑም ግለሰቦችን በቦርዱ የመረጃ ቋት ውስጥ ባላቸው ስልክ ቁጥር በመደወል ለማግኘት የተደረገው ጥረት ስልካቸው ሊሰራ ባለመቻሉ ምክንያት ሊሳካ አልቻለም። በዚህ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘረው ግለሰቦች ከፖለቲካ ፓርቲያችሁ መልቀቃቸሁን ለፓርቲያችሁ እንድታሳውቁ እና መልቀቃችሁን የሚገልጽ ሰነድ ለቦርዱ እንድትልኩ እንጠይቃለን።

የእጩ ስም ዝርዝር ለማየት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post