የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት በነሐሴ 15 ቀን 2014 ዓ.ም. ለሦስተኛ ጊዜ ተጠርቶ አቶ አምሀ ዳኜው ምክትል ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ ያሣለፈውን ውሣኔና ጠቅላላ ጉባዔ ለመጥራት የሄደበት ሂደት አስመልክቶ ፓርቲው ያቀረበውን ሠነድ ከዐዋጁና ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ አንጻር በመመርመር ሂደቱ የተሟላ በመሆኑ ቦርዱ ተቀብሎታል። በመሆኑም ፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔውን የሚያካሂድበትን ቀን በመቁረጥ ለቦርዱ በማሳወቅ እንዲያከናውን ቦርዱ ወሥኗል።

ደብዳቤው እዚህ ላይ ያገኙታል

ማስታወቂያ
ኅዳር 16 ቀን 2015 ዓ.ም.