የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኔ 17 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ የሚዲያ ማብራሪያ ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:30 ስካይላይት ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

•በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣

•የቦርዱን ልዩ የዘገባ ባጅ ፊት ለፊት ማንጠልጠል

•ከአንድ ሚዲያ ሁለት ባለሞያዎች (የፎቶ/የቪዲዮ ባለሙያን ጨምሮ) ብቻ መሣተፍ ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ማስታወቂያ
ሰኔ 17 ቀን 2013 ዓ.ም