1. ድምፅ ለመስጠት በተመዘገበችበት የምርጫ ጣቢያ የተገኘች መራጭ፡-

ሀ) የመራጮች ምዝገባ መታወቂያ ካርድ ያላት፣

ለ) የማንነት ማረጋገጫ መታወቂያ ወይም በመራጮች ምዝገባ ወቅት የተረጋገጠበት ሌላ ሰነድ ያላት፣ወይም ማንነትዋ በምርጫ ምዝገባ ወቅት በምስክሮች ስለመረጋገጡ

በመራጮች መዝገብ ላይ የሰፈረላት፣

ሐ) የመራጮች መዝገብ ላይ ስሟ የሰፈረ፣

መ) ድምፅ ያልሰጠች መሆኑ ሲረጋገጥ ድምጿን የመስጠት መብት አላት

2. የመራጮች ምዝገባ መታወቂያ የጠፋባት መራጭ ጉዳዩን ለምርጫ ጣቢያው በማስረዳት ማንነቷ እንዲሁም በመዝገቡ ላይ ስሟ የሰፈረና ያልመረጠች መሆኑ ሲረጋገጥ ጉዳዩ በቃለ ጉባኤ ተይዞ እንድትመርጥ ይደረጋል፡፡

ማስታወቂያ
ሰኔ 13 ቀን 2013 ዓ.ም