ሰኞ ሰኔ 14 ቀን ለሚከናውነው አጠቃላይ ምርጫ የፓርቲ ወኪሎችን እውቅና ባጅ የመስጠት ስራ እያከናወናችሁ እንደሆነ ይታወቃል። ካለው አጭር ጊዜ አንጻር የእጩ ወኪሎች ባጅ መስጠትን እስከ ነገ ማታ ሰኔ 13 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ እንድታከናውኑ እናሳስባለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኦፕሬሽንስ የስራ ክፍል

ማስታወቂያ
ሰኔ12 ቀን 2013 ዓ.ም