የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ የእጩዎች ምዝገባን እያከናወነ እንዳለ ይታወቃል። በዚህም መሰረት የመጀመሪያ ዙር የእጩ ምዝገባ የሚከናውንባቸው ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች ማለትም

የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር

የድሬደዋ ከተማ መስተዳድር

የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልል

የጋምቤላ ብሔራዊ ክልል

ሃሪሪ ብሔራዊ ክልል ለእጩዎች ምዝገባ የተቀመጠው የጊዜ ገደብ መሰረት የካቲት 08- 21 ድረስ እንደሚከናወን ማሳወቁ ይታወቃል።

ቦርዱ የእጩዎች ምዝገባ ሂደትን በመገምገም የምርጫ ክልል ቢሮዎች ለመከፈት በመዘግየታቸው፣ የትራንስፓርት መጓተት የተወሰኑ የምርጫ ክልሎች ላይ የምዝገባ ቀንን በማራዘሙ እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ ምክንያቶች እጩዎችን ለመመዝገብ ችግር ስላጋጠመን ይራዘምልን ብለው ጠይቀዋል በመሆኑም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከላይ የተጠቀሱትን አሳማኝ ምክንያቶች በማየት የመጀመሪያ ዙር ምዝገባ በጀመሩት ከላይ በተጠቀሱት ክልሎች/የከተማ መስተዳድሮች ላይ የሚካሄደው የእጩዎች ምዝገባ 4 ቀናት ያህል እስከ የካቲት 25 ቀን 2013 . ድረስ መራዘሙን ያሳውቃል።