የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእጩዎች ምዝገባን ከየካቲት 08 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በሁለት ዙሮች ሲያከናውን እንደነበር እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች ተጨማሪ ቀናት በመጨመር እና የፓርቲዎችን አቤቱታዎች በመፍታት ሲያከናውን ቆይቷል።

በዚህም መሰረት የእጩዎች ምዝገባ ትላንትና የካቲት 30 ቀን 2013 ዓ.ም በይፋ ተጠናቋል። በመሆኑም በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቢሮዎች ችግር የተነሳ በልዩ ሁኔታ የሚታይ ካልሆነ በስተቀር ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ የእጩዎች ምዝገባ መዘጋቱን እየገለጸ አጠቃላይ የጸደቁ የእጩዎች ዝርዝርን በቅርቡ ይፋ የሚያደርግ ይሆናል።