Skip to main content

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የመራጮች ምዝገባ ጊዜ ተራዘመ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የመራጮች ምዝገባ በኢንተርኔት እንደሚከናወን ማሳወቁ እንዲሁም ይህንን ተከትሎ ምዝገባ ሲከናወን እንደነበር ይታወቃል። በየምርጫ ጣቢያዎቹ የሚደገረው መራጮች ምዝገባ ቢጠናቀቅም ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ተጨማሪ የምዝገባ ጊዜ መሰጠት እንዳለበት ቦርዱ ወስኗል። በዚህም መሰረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች እስከ ግንቦት 17 ቀን 2013 ድረስ https://www.ovrs.gov.et በሚገኘው የመመዝገቢያ ሊንክ በመጠቀም እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።

የፓለቲካ ፓርቲዎች፣ ሚዲያዎች እንዲሁም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትም ይህንን የኦንላየን ምዝገባ በማስታወስ ምዝገባቸውን እንዲያከናውኑ እንድታደርጉ የተለመደ ትብብራችሁን እንጠይቃለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ግንቦት 11 ቀን 2013 ዓ.ም

Share this post