Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቦርዱ ያወጣቸውን መመሪያዎች አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ለሁለት የተለያዩ ቀናት ያደረገውን ምክክር አጠናቀቀ

ሕዳር 03 እና 04 ቀን 2013 አም በተከናወኑት ምክክሮች ውይይት የተደረገባቸው መመሪዎች

- የእጩ ተወዳዳሪዎች ምዝገባ አፈፃፀም መመሪያ
-የድጋፍ ፊርማ አሰባሰብ እና መለያ ምልክት አመራረጥ መመሪያ
-የምርጫ ውድድር ቅስቀሳ ስነ ምግባር መመሪያ
-የአለምአቀፍ የምርጫ ታዛቢዎች ፍቃድ አሰጣጥ፣ የአሠራር ሥርዓት እና የሥነ ምግባር መመሪያዎች ሲሆኑ ፓለቲካ ፓርቲዎች ከህግ፣ ከልምድ እና ከቀድሞ አሰራሮች በመነሳት የተለያዩ ግብአቶችን ሰጥተዋል፡፡

ምክክሩ ቦርዱ የፓለቲካ ፓርቲዎችን ግብአት ለማካተት ከሚያደርጋቸው ተከታታይ ምክክሮች መካከል አንዱ ሲሆን በተከታዩ ሳምንትም በሌሎች መመሪያዎች ላይ በሚደረግ ውይይት የሚቀጥል ይሆናል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post