የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ለማስፈጸም ህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚዎች ምልመላ እያከናወነ እንደነበር ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ምዝገባ ሲያከናውን በቆየባቸው ቀናት የተገኘው የአመልካቾች ቁጥር መጨመር የተነሳ የህዝውሳኔ አስፈጻሚዎች ምዝገባን ዛሬ ያጠናቅቃል፡፡ በመሆኑም ለማመልከት የምትፈልጉ ዛሬ አርብ ጥቅምት 7 ቀን 2012 አ.ም እስከስራ ሰአት ማጠናቀቂያ (11 ሰአት) ድረስ ንፋስ ስልክ ቡና ቦርድ ጋር የሚገኘው የቦርዱ ማሰልጠኛ ማእከል ማመልከት የምትችሉ ሲሆን የማመልከቻው የመጨረሻ ቀን ዛሬ ነው፡፡

 

የጥሪ ማስታወቂያ
ጥቅምት 7 ቀን 2012 ዓ.ም.