የሲዳማ ክልልነት ህዝበ ውሳኔ አፈጻጸም መርሃ-ግብር መሰረት የቅስቀሳ ጊዜ ከመስከረም 23 - 28 ቀን 2012 ዓ.ም በሚል ታቅዶ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ ነገር ግን የህዝበ ውሳኔ ቅስቀሳው የመራጮች ምዝገባ ከሚደረግበት ጊዜ ጋር የተቀራረበ ቢሆን ይሻላል በሚል ስለታመነበት የቅስቀሳ መርሃግብሩ ከጥቅምት 18 - 22 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት እንዲሆን ተብሎ ተሻሽሏል፡፡ ቦርዱ በአፈጻጸም ጉዳዮች የተነሳ የሚኖሩ የቀናት ለውጥና መሸጋሸጎችን ለወደፊትም ይፋ የሚያደርግ ይሆናል፡፡


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ማስታወቂያ