Skip to main content

የሚዲያዎች ዘገባ ማስተካከያ

ሐምሌ 18 ቀን 2011 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያለበትን ከፍተኛ የሥራ ጫና፣ የአቅም ውስነንነት እና የሪፎርም ሥራ መደራረብ የተነሳ በዚህ ዓመት መደረግ የነበረበትን የአካባቢ ምርጫ እና የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ ምክር ቤቶች ምርጫ ማካሄድ እንደማይችል ለኢፌዴሪ ተወካዮች ምክር ቤት በጽሁፍ የገለጸ ቢሆንም ምርጫዎቹ ከሚቀጥለው አገራዊ ምርጫዎች ጋር እንዲካሄዱ ምክረሃሳብ ያቀረበውም ሆነ ውሳኔ ያሳለፈው የተወካዮች ምክር ቤት ነው። በመሆኑም ቦርዱ የአካባቢ ምርጫም ሆነ የሁለቱ ከተማ ምክር ቤቶች ምርጫ ከአጠቃላይ ምርጫ ጋር መካሄድ አለባቸው የሚል የውሳኔ ሀሳብ አቅርቧል የሚለው የሚዲያዎች ሪፓርት ማስተካከያ እንዲደረግበት እንጠይቃለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የሚዲያዎች ሪፓርት ማስተካከያ


 

Share this post